92) Sūrat Al-Layl

Printed format

92) سُورَة اللَيل

Wa Al-Layli 'Idhā Yaghshá 092-001 በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡ وَاللَّيْلِ إِذَا يَغْشَى
Wa An-Nahāri 'Idhā Tajallá 092-002 በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡ وَال‍‍ن‍ّ‍‍َه‍‍َ‍ا‍ر‍ِ إِذَا تَجَلَّى
Wa Mā Khalaqa Adh-Dhakara Wa Al-'Unthá 092-003 ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡ وَمَا خَلَقَ ا‍لذَّكَرَ وَا‍لأُ‍ن‍‍ْثَى
'Inna Sa`yakum Lashattá 092-004 ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ سَعْيَكُمْ لَشَتَّى
Fa'ammā Man 'A`ţá Wa Attaqá 092-005 የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡ فَأَ‍مّ‍‍َا مَنْ أَعْطَى وَا‍تَّقَى
Wa Şaddaqa Bil-Ĥusná 092-006 በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤ وَصَدَّقَ بِ‍‍ا‍لْحُسْنَى
Fasanuyassiruhu Lilyusrá 092-007 ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْيُسْرَى
Wa 'Ammā Man Bakhila Wa Astaghná 092-008 የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤ وَأَ‍مّ‍‍َا مَ‍‍ن‍ْ بَخِلَ وَا‍سْتَغْنَى
Wa Kadhdhaba Bil-Ĥusná 092-009 በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤ وَكَذَّبَ بِ‍‍ا‍لْحُسْنَى
Fasanuyassiruhu Lil`usrá 092-010 ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡ فَسَنُيَسِّرُهُ لِلْعُسْرَى
Wa Mā Yughnī `Anhu Māluhu 'Idhā Taraddá 092-011 በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡ وَمَا يُغْنِي عَنْهُ مَالُهُ إِذَا تَرَدَّى
'Inna `Alaynā Lalhudá 092-012 ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡ إِ‍نّ‍‍َ عَلَيْنَا لَلْهُدَى
Wa 'Inna Lanā Lal'ākhirata Wa Al-'Ū 092-013 መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َ لَنَا لَلآخِرَةَ وَا‍لأ‍ُ‍ولَى
Fa'andhartukum Nārāan Talažžá 092-014 የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡ فَأَ‍ن‍‍ْذَرْتُكُمْ نَارا‍ً تَلَظَّى
Lā Yaşlāhā 'Illā Al-'Ashqá 092-015 ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡ لاَ يَصْلاَهَ‍‍ا إِلاَّ ا‍لأَشْقَى
Al-Ladhī Kadhdhaba Wa Tawallá 092-016 ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡ ا‍لَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّى
Wa Sayujannabuhā Al-'Atqá 092-017 አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡ وَسَيُجَ‍‍ن‍ّ‍‍َبُهَا ا‍لأَتْقَى
Al-Ladhī Yu'utī Mālahu Yatazakká 092-018 ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡ ا‍لَّذِي يُؤْتِي مَالَهُ يَتَزَكَّى
Wa Mā Li'ĥadin `Indahu Min Ni`matin Tuj 092-019 ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡ وَمَا لِأحَدٍ عِ‍‍ن‍‍ْدَهُ مِ‍‍ن‍ْ نِعْمَة‍‍‍ٍ تُ‍‍ج‍‍ْزَى
'Illā Abtighā'a Wajhi Rabbihi Al-'A`lá 092-020 ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡ إِلاَّ ا‍ب‍‍ْتِغ‍‍َ‍ا‍ءَ وَج‍‍ْهِ رَبِّهِ ا‍لأَعْلَى
Wa Lasawfa Yarđá 092-021 ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡ وَلَسَوْفَ يَرْضَى
Next Sūrah