85) Sūrat Al-Burūj

Printed format

85) سُورَة البُرُوج

Wa As-Samā'i Dhāti Al-Burūji 085-001 የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡ وَالسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ ذ‍َا‍تِ ا‍لْبُر‍ُو‍ج‍ِ
Wa Al-Yawmi Al-Maw`ūdi 085-002 በተቀጠረው ቀንም፤ وَالْيَوْمِ ا‍لْمَوْع‍‍ُ‍و‍د‍ِ
Wa Shāhidin Wa Mash/hūdin 085-003 በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡ وَشَاهِد‍ٍ وَمَشْه‍‍ُ‍و‍د‍ٍ
Qutila 'Aşĥābu Al-'Ukhdūdi 085-004 የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡ قُتِلَ أَصْح‍‍َ‍ا‍بُ ا‍لأُخْد‍ُو‍د‍ِ
An-Nāri Dhāti Al-Waqūdi 085-005 የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡ ا‍ل‍‍ن‍ّ‍‍َ‍ا‍ر‍ِ ذ‍َا‍تِ ا‍لْوَق‍‍ُ‍و‍د‍ِ
'Idh Hum `Alayhā Qu`ūdun 085-006 እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡ إِذْ هُمْ عَلَيْهَا قُع‍‍ُ‍و‍د‍ٌ
Wa Hum `Alá Mā Yaf`alūna Bil-Mu'uminīna Shuhūdun 085-007 እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡ وَهُمْ عَلَى مَا يَفْعَل‍‍ُ‍و‍نَ بِ‍‍ا‍لْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ شُه‍‍ُ‍و‍د‍ٌ
Wa Mā Naqamū Minhum 'Illā 'An Yu'uminū Bil-Lahi Al-`Azīzi Al-Ĥamīdi 085-008 ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡ وَمَا نَقَمُو‍‍ا‍ مِنْهُمْ إِلاَّ أَ‍ن‍ْ يُؤْمِنُو‍‍ا‍ بِ‍‍ا‍للَّهِ ا‍لْعَز‍ِي‍زِ ا‍لْحَم‍‍ِ‍ي‍‍د‍ِ
Al-Ladhī Lahu Mulku As-Samāwāti Wa Al-'Arđi Wa Allāhu `Alá Kulli Shay'in Shahīdun 085-009 በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡ ا‍لَّذِي لَهُ مُلْكُ ا‍لسَّمَاو‍َا‍تِ وَا‍لأَرْضِ وَا‍للَّهُ عَلَى كُلِّ شَيْء‍ٍ شَه‍‍ِ‍ي‍‍د‍ٌ
'Inna Al-Ladhīna Fatanū Al-Mu'uminīna Wa Al-Mu'umināti Thumma Lam Yatūbū Falahum `Adhābu Jahannama Wa Lahum `Adhābu Al-Ĥarīqi 085-010 እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ فَتَنُو‍‍ا‍ ا‍لْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ وَا‍لْمُؤْمِن‍‍َ‍ا‍تِ ثُ‍‍م‍ّ‍‍َ لَمْ يَتُوبُو‍‍ا‍ فَلَهُمْ عَذ‍َا‍بُ جَهَ‍‍ن‍ّ‍‍َمَ وَلَهُمْ عَذ‍َا‍بُ ا‍لْحَ‍‍ر‍‍ِي‍‍ق‍ِ
'Inna Al-Ladhīna 'Āmanū Wa `Amilū Aş-Şāliĥāti Lahum Jannātun Tajrī Min Taĥtihā Al-'Anhāru Dhālika Al-Fawzu Al-Kabīru 085-011 እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ آمَنُو‍‍ا‍ وَعَمِلُو‍‍ا‍ ا‍لصَّالِح‍‍َ‍ا‍تِ لَهُمْ جَ‍‍ن‍ّ‍‍َ‍ا‍ت‍‍‍ٌ تَ‍‍ج‍‍ْ‍‍ر‍‍ِي مِ‍‍ن‍ْ تَحْتِهَا ا‍لأَنْه‍‍َ‍ا‍رُ ذَلِكَ ا‍لْفَوْزُ ا‍لْكَب‍‍ِ‍ي‍‍ر‍ُ
'Inna Baţsha Rabbika Lashadīdun 085-012 የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ بَ‍‍ط‍‍ْشَ رَبِّكَ لَشَد‍ِي‍‍د‍ٌ
'Innahu Huwa Yubdi'u Wa Yu`īdu 085-013 እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡ إِ‍نّ‍‍َهُ هُوَ يُ‍‍ب‍‍ْدِئُ وَيُع‍‍ِ‍ي‍‍د‍ُ
Wa Huwa Al-Ghafūru Al-Wadūdu 085-014 እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡ وَهُوَ ا‍لْغَف‍‍ُ‍و‍رُ ا‍لْوَد‍ُو‍د‍ُ
Dhū Al-`Arshi Al-Majīdu 085-015 የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡ ذُو ا‍لْعَرْشِ ا‍لْمَج‍‍ِ‍ي‍‍د‍ُ
Fa``ālun Limā Yurīdu 085-016 የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡ فَعّ‍‍َ‍ا‍ل‍‍‍ٌ لِمَا يُ‍‍ر‍‍ِي‍‍د‍ُ
Hal 'Atāka Ĥadīthu Al-Junūdi 085-017 የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን? هَلْ أَت‍‍َ‍ا‍كَ حَد‍ِي‍ثُ ا‍لْجُن‍‍ُ‍و‍د‍ِ
Fir`awna Wa Thamūda 085-018 የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡ فِرْعَوْنَ وَثَم‍‍ُ‍و‍د‍َ
Bali Al-Ladhīna Kafarū Fī Takdhībin 085-019 በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡ بَلِ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ كَفَرُوا‍ فِي تَكْذ‍ِي‍‍ب‍‍ٍ
Wa Allāhu Min Warā'ihim Muĥīţun 085-020 አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡ وَاللَّهُ مِ‍‍ن‍ْ وَر‍َا‍ئِهِ‍‍م‍ْ مُح‍‍ِ‍ي‍‍ط‍‍ٌ
Bal Huwa Qur'ānun Majīdun 085-021 ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡ بَلْ هُوَ قُرْآن‍‍‍ٌ مَج‍‍ِ‍ي‍‍د‍ٌ
Fī Lawĥin Maĥfūžin 085-022 የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡ فِي لَوْح‍‍‍ٍ مَحْف‍‍ُ‍و‍ظ‍‍‍ٍ
Next Sūrah