84) Sūrat Al-'Inshiqāq

Printed format

84) سُورَة الإنشِقَاق

'Idhā As-Samā'u Anshaqqat 084-001 ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤ إِذَا ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءُ ا‍ن‍شَقَّتْ
Wa 'Adhinat Lirabbihā Wa Ĥuqqat 084-002 ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤ وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
Wa 'Idhā Al-'Arđu Muddat 084-003 ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤ وَإِذَا ا‍لأَرْضُ مُدَّتْ
Wa 'Alqat Mā Fīhā Wa Takhallat 084-004 በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤ وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ
Wa 'Adhinat Lirabbihā Wa Ĥuqqat 084-005 ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡ وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
Yā 'Ayyuhā Al-'Insānu 'Innaka Kādiĥun 'Ilá Rabbika Kadĥāan Famulāqīhi 084-006 አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡ ي‍َا‍أَيُّهَا ا‍لإِن‍س‍‍َ‍ا‍نُ إِ‍نّ‍‍َكَ كَادِح‍‍‍ٌ إِلَى رَبِّكَ كَ‍‍د‍‍ْحا‍ً فَمُلاَق‍‍ِ‍ي‍هِ
Fa'ammā Man 'Ūtiya Kitābahu Biyamīnihi 084-007 መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤ فَأَ‍مّ‍‍َا مَنْ أ‍ُ‍وتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ
Fasawfa Yuĥāsabu Ĥisābāan Yasīrāan 084-008 በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡ فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابا‍ً يَسِيرا‍ً
Wa Yanqalibu 'Ilá 'Ahlihi Masrūrāan 084-009 ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡ وَيَ‍‍ن‍قَلِبُ إِلَى أَهْلِهِ مَسْرُورا‍ً
Wa 'Ammā Man 'Ūtiya Kitābahu Warā'a Žahrihi 084-010 መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤ وَأَ‍مّ‍‍َا مَنْ أ‍ُ‍وتِيَ كِتَابَهُ وَر‍َا‍ءَ ظَهْ‍‍ر‍‍ِهِ
Fasawfa YadThubūrāan 084-011 (ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡ فَسَوْفَ يَ‍‍د‍‍ْعُو ثُبُورا‍ً
Wa Yaşlá Sa`īrāan 084-012 የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡ وَيَصْلَى سَعِيرا‍ً
'Innahu Kāna Fī 'Ahlihi Masrūrāan 084-013 እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡ إِ‍نّ‍‍َهُ ك‍‍َ‍ا‍نَ فِ‍‍ي‍ أَهْلِهِ مَسْرُورا‍ً
'Innahu Žanna 'An Lan Yaĥūra 084-014 እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡ إِ‍نّ‍‍َهُ ظَ‍‍ن‍ّ‍‍َ أَ‍ن‍ْ لَ‍‍ن‍ْ يَح‍‍ُ‍و‍رَ
Balá 'Inna Rabbahu Kāna Bihi Başīrāan 084-015 አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡ بَلَى إِ‍نّ‍‍َ رَبَّهُ ك‍‍َ‍ا‍نَ بِهِ بَصِيرا‍ً
Falā 'Uqsimu Bish-Shafaqi 084-016 አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡ فَلاَ أُ‍ق‍‍ْسِمُ بِ‍‍ا‍لشَّفَ‍‍ق‍ِ
Wa Al-Layli Wa Mā Wasaqa 084-017 በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤ وَاللَّيْلِ وَمَا وَسَ‍‍ق‍َ
Wa Al-Qamari 'Idhā Attasaqa 084-018 በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡ وَالْقَمَ‍‍ر‍ِ إِذَا ا‍تَّسَ‍‍ق‍َ
Latarkabunna Ţabaqāan `An Ţabaqin 084-019 ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡ لَتَرْكَبُ‍‍ن‍ّ‍‍َ طَبَقاً عَ‍‍ن‍ْ طَبَ‍‍ق‍‍ٍ
Famā Lahum Lā Yu'uminūna 084-020 የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው? فَمَا لَهُمْ لاَ يُؤْمِن‍‍ُ‍و‍نَ
Wa 'Idhā Quri'a `Alayhimu Al-Qur'ānu Lā Yasjudūna 084-021 በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) وَإِذَا قُ‍‍ر‍‍ِئَ عَلَيْهِمُ ا‍لْقُرْآنُ لاَ يَسْجُد‍ُو‍نَ
Bali Al-Ladhīna Kafarū Yukadhdhibūna 084-022 በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡ بَلِ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ كَفَرُوا‍ يُكَذِّب‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Allāhu 'A`lamu Bimā Yū`ūna 084-023 አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡ وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوع‍‍ُ‍و‍نَ
Fabashshirhum Bi`adhābin 'Alīmin 084-024 በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡ فَبَشِّرْهُ‍‍م‍ْ بِعَذ‍َا‍بٍ أَل‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
'Illā Al-Ladhīna 'Āmanū Wa `Amilū Aş-Şāliĥāti Lahum 'Ajrun Ghayru Mamnūnin 084-025 ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡ إِلاَّ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ آمَنُو‍‍ا‍ وَعَمِلُو‍‍ا‍ ا‍لصَّالِح‍‍َ‍ا‍تِ لَهُمْ أَ‍ج‍‍ْرٌ غَيْرُ مَمْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
Next Sūrah