82) Sūrat Al-'Infiţār

Printed format

82) سُورَة الإنفِطَار

'Idhā As-Samā'u Anfaţarat 082-001 ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤ إِذَا ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءُ ا‍ن‍فَطَرَتْ
Wa 'Idhā Al-Kawākibu Antatharat 082-002 ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤ وَإِذَا ا‍لْكَوَاكِبُ ا‍ن‍تَثَرَتْ
Wa 'Idhā Al-Biĥāru Fujjirat 082-003 ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤ وَإِذَا ا‍لْبِح‍‍َ‍ا‍رُ فُجِّرَتْ
Wa 'Idhā Al-Qubūru Bu`thirat 082-004 መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤ وَإِذَا ا‍لْقُب‍‍ُ‍و‍رُ بُعْثِرَتْ
`Alimat Nafsun Mā Qaddamat Wa 'Akhkharat 082-005 ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡ عَلِمَتْ نَفْس‍‍‍ٌ مَا قَدَّمَتْ وَأَخَّرَتْ
Yā 'Ayyuhā Al-'Insānu Mā Gharraka Birabbika Al-Karīmi 082-006 አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ? ي‍َا‍أَيُّهَا ا‍لإِن‍س‍‍َ‍ا‍نُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ا‍لْكَ‍‍ر‍‍ِي‍مِ
Al-Ladhī Khalaqaka Fasawwāka Fa`adalaka 082-007 በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡ ا‍لَّذِي خَلَقَكَ فَسَوّ‍َا‍كَ فَعَدَلَكَ
Fī 'Ayyi ŞūratinShā'a Rakkabaka 082-008 በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡ فِ‍‍ي‍ أَيِّ صُورَة‍‍‍ٍ مَا ش‍‍َ‍ا‍ءَ رَكَّبَكَ
Kallā Bal Tukadhdhibūna Bid-Dīni 082-009 ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡ كَلاَّ بَلْ تُكَذِّب‍‍ُ‍و‍نَ بِ‍‍ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Wa 'Inna `Alaykum Laĥāfižīna 082-010 በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤ وَإِ‍نّ‍‍َ عَلَيْكُمْ لَحَافِظ‍‍ِ‍ي‍نَ
Kirāmāan Kātibīna 082-011 የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡ كِرَاما‍ً كَاتِب‍‍ِ‍ي‍نَ
Ya`lamūna Mā Taf`alūna 082-012 የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡ يَعْلَم‍‍ُ‍و‍نَ مَا تَفْعَل‍‍ُ‍و‍نَ
'Inna Al-'Abrāra Lafī Na`īmin 082-013 እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لأَ‍ب‍‍ْر‍َا‍رَ لَفِي نَع‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
Wa 'Inna Al-Fujjāra Lafī Jaĥīmin 082-014 ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َ ا‍لْفُجّ‍‍َ‍ا‍رَ لَفِي جَح‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
Yaşlawnahā Yawma Ad-Dīni 082-015 በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡ يَصْلَوْنَهَا يَوْمَ ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Wa Mā Hum `Anhā Bighā'ibīna 082-016 እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡ وَمَا هُمْ عَنْهَا بِغ‍‍َ‍ا‍ئِب‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Mā 'Adrāka Mā Yawmu Ad-Dīni 082-017 የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ? وَمَ‍‍ا‍ أَ‍د‍‍ْر‍َا‍كَ مَا يَوْمُ ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Thumma Mā 'Adrāka Mā Yawmu Ad-Dīni 082-018 ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ? ثُ‍‍م‍ّ‍‍َ مَ‍‍ا‍ أَ‍د‍‍ْر‍َا‍كَ مَا يَوْمُ ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Yawma Lā Tamliku Nafsun Linafsin Shay'āan Wa Al-'Amru Yawma'idhin Lillahi 082-019 (እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡ يَوْمَ لاَ تَمْلِكُ نَفْس‍‍‍ٌ لِنَفْس‍‍‍ٍ شَيْئا‍ً وَا‍لأَمْرُ يَوْمَئِذ‍ٍ لِلَّهِ
Next Sūrah