'Idhā Ash-Shamsu Kūwirat | 081-001 ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤ | إِذَا الشَّمْسُ كُوِّرَتْ |
Wa 'Idhā An-Nujūmu Ankadarat | 081-002 ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤ | وَإِذَا النُّجُومُ انكَدَرَتْ |
Wa 'Idhā Al-Jibālu Suyyirat | 081-003 ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤ | وَإِذَا الْجِبَالُ سُيِّرَتْ |
Wa 'Idhā Al-`Ishāru `Uţţilat | 081-004 የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤ | وَإِذَا الْعِشَارُ عُطِّلَتْ |
Wa 'Idhā Al-Wuĥūshu Ĥushirat | 081-005 እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤ | وَإِذَا الْوُحُوشُ حُشِرَتْ |
Wa 'Idhā Al-Biĥāru Sujjirat | 081-006 ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤ | وَإِذَا الْبِحَارُ سُجِّرَتْ |
Wa 'Idhā An-Nufūsu Zūwijat | 081-007 ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤ | وَإِذَا النُّفُوسُ زُوِّجَتْ |
Wa 'Idhā Al-Maw'ūdatu Su'ilat | 081-008 በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤ | وَإِذَا الْمَوْءُودَةُ سُئِلَتْ |
Bi'ayyi Dhanbin Qutilat | 081-009 በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤ | بِأَيِّ ذَنْبٍ قُتِلَتْ |
Wa 'Idhā Aş-Şuĥufu Nushirat | 081-010 ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤ | وَإِذَا الصُّحُفُ نُشِرَتْ |
Wa 'Idhā As-Samā'u Kushiţat | 081-011 ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤ | وَإِذَا السَّمَاءُ كُشِطَتْ |
Wa 'Idhā Al-Jaĥīmu Su``irat | 081-012 ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤ | وَإِذَا الْجَحِيمُ سُعِّرَتْ |
Wa 'Idhā Al-Jannatu 'Uzlifat | 081-013 ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤ | وَإِذَا الْجَنَّةُ أُزْلِفَتْ |
`Alimat Nafsun Mā 'Aĥđarat | 081-014 ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤ | عَلِمَتْ نَفْسٌ مَا أَحْضَرَتْ |
Falā 'Uqsimu Bil-Khunnasi | 081-015 ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡ | فَلاَ أُقْسِمُ بِالْخُنَّسِ |
Al-Jawāri Al-Kunnasi | 081-016 ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡ | الْجَوَارِ الْكُنَّسِ |
Wa Al-Layli 'Idhā `As`asa | 081-017 በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤ | وَاللَّيْلِ إِذَا عَسْعَسَ |
Wa Aş-Şubĥi 'Idhā Tanaffasa | 081-018 በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡ | وَالصُّبْحِ إِذَا تَنَفَّسَ |
'Innahu Laqawlu Rasūlin Karīmin | 081-019 እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡ | إِنَّهُ لَقَوْلُ رَسُولٍ كَرِيمٍ |
Dhī Qūwatin `Inda Dhī Al-`Arshi Makīnin | 081-020 የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡ | ذِي قُوَّةٍ عِنْدَ ذِي الْعَرْشِ مَكِينٍ |
Muţā`in Thamma 'Amīnin | 081-021 በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡ | مُطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ |
Wa Mā Şāĥibukum Bimajnūnin | 081-022 ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡ | وَمَا صَاحِبُكُمْ بِمَجْنُونٍ |
Wa Laqad Ra'āhu Bil-'Ufuqi Al-Mubīni | 081-023 በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡ | وَلَقَدْ رَآهُ بِالأُفُقِ الْمُبِينِ |
Wa Mā Huwa `Alá Al-Ghaybi Biđanīnin | 081-024 እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡ | وَمَا هُوَ عَلَى الْغَيْبِ بِضَنِينٍ |
Wa Mā Huwa Biqawli Shayţānin Rajīmin | 081-025 እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡ | وَمَا هُوَ بِقَوْلِ شَيْطَانٍ رَجِيمٍ |
Fa'ayna Tadh/habūna | 081-026 ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ? | فَأَيْنَ تَذْهَبُونَ |
'In Huwa 'Illā Dhikrun Lil`ālamīna | 081-027 እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ | إِنْ هُوَ إِلاَّ ذِكْرٌ لِلْعَالَمِينَ |
Liman Shā'a Minkum 'An Yastaqīma | 081-028 ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡ | لِمَنْ شَاءَ مِنْكُمْ أَنْ يَسْتَقِيمَ |
Wa Mā Tashā'ūna 'Illā 'An Yashā'a Al-Lahu Rabbu Al-`Ālamīna | 081-029 የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡ | وَمَا تَشَاءُونَ إِلاَّ أَنْ يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ |