`Amma Yatasā'alūna  | 078-001 ከምን ነገር ይጠያየቃሉ? | عَمَّ يَتَسَاءَلُونَ |
`Ani An-Naba'i Al-`Ažīmi  | 078-002 ከታላቁ ዜና (ከቁርኣን ይጠያየቃሉ)፡፡ | عَنِ النَّبَإِ الْعَظِيمِ |
Al-Ladhī Hum Fīhi Mukhtalifūna  | 078-003 ከዚያ እነርሱ በእርሱ የተለያዩበት ከኾነው፡፡ | الَّذِي هُمْ فِيهِ مُخْتَلِفُونَ |
Kallā Saya`lamūna  | 078-004 ይከልከሉ፤ ወደፊት (የሚደርስበቸውን) በእርግጥ ያውቃሉ፡፡ | كَلاَّ سَيَعْلَمُونَ |
Thumma Kallā Saya`lamūna  | 078-005 ከዚያም ይከልከሉ፤ ወደፊት ያውቃሉ፡፡ | ثُمَّ كَلاَّ سَيَعْلَمُونَ |
'Alam Naj`ali Al-'Arđa Mihādāan  | 078-006 ምድርን ምንጣፍ አላደረግንምን? | أَلَمْ نَجْعَلِ الأَرْضَ مِهَاداً |
Wa Al-Jibāla 'Awtādāan  | 078-007 ጋራዎችንም ችካሎች አላደረግንምን? | وَالْجِبَالَ أَوْتَاداً |
Wa Khalaqnākum 'Azwājāan  | 078-008 ብዙ ዓይነቶችም አድርገን ፈጠርናችሁ፡፡ | وَخَلَقْنَاكُمْ أَزْوَاجاً |
Wa Ja`alnā Nawmakum Subātāan  | 078-009 እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን፡፡ | وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتاً |
Wa Ja`alnā Al-Layla Libāsāan  | 078-010 ሌሊቱንም ልባስ አደረግን፡፡ | وَجَعَلْنَا اللَّيْلَ لِبَاساً |
Wa Ja`alnā An-Nahāra Ma`āshāan  | 078-011 ቀኑንም (ለኑሮ) መስሪያ አደረግን፡፡ | وَجَعَلْنَا النَّهَارَ مَعَاشاً |
Wa Banaynā Fawqakum Sab`āan Shidādāan  | 078-012 ከበላያችሁም ሰባትን ብርቱዎች (ሰማያት) ገነባን፡፡ | وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعاً شِدَاداً |
Wa Ja`alnā Sirājāan Wa Hhājāan  | 078-013 አንጸባራቂ ብርሃንንም አደረግን፡፡ | وَجَعَلْنَا سِرَاجاً وَهَّاجاً |
Wa 'Anzalnā Mina Al-Mu`şirāti Mā'an Thajjājāan  | 078-014 ከአረገዙት ደመናዎችም ተንቧቢ ውሃን አወረድን፡፡ | وَأَنزَلْنَا مِنَ الْمُعْصِرَاتِ مَاءً ثَجَّاجاً |
Linukhrija Bihi Ĥabbāan Wa Nabātāan  | 078-015 በእርሱ እኽልንና ቅጠላ ቅጠልን እናወጣ ዘንድ (አወረድን)፡፡ | لِنُخْرِجَ بِهِ حَبّاً وَنَبَاتاً |
Wa Jannātin 'Alfāfāan  | 078-016 የተቆላለፉ አትክልቶችንም፡፡ | وَجَنَّاتٍ أَلْفَافاً |
'Inna Yawma Al-Faşli Kāna Mīqātāan  | 078-017 የመለያው ቀን የተወሰነ ጊዜ ነው፡፡ | إِنَّ يَوْمَ الْفَصْلِ كَانَ مِيقَاتاً |
Yawma Yunfakhu Fī Aş-Şūri Fata'tūna 'Afwājāan  | 078-018 በቀንዱ በሚነፋና የተለያዩ ጭፍሮች ኾናችሁ በምትመጡ ቀን ነው፡፡ | يَوْمَ يُنفَخُ فِي الصُّورِ فَتَأْتُونَ أَفْوَاجاً |
Wa Futiĥati As-Samā'u Fakānat 'Abwābāan  | 078-019 ሰማይም በምትከፈትና (ባለ) ደጃፎችም በምትኾንበት፡፡ | وَفُتِحَتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ أَبْوَاباً |
Wa Suyyirati Al-Jibālu Fakānat Sarābāan  | 078-020 ጋራዎችም በሚነዱበት (እንደ) ሲሪብዱም በሚኾኑበት (ቀን) ነው፡፡ | وَسُيِّرَتِ الْجِبَالُ فَكَانَتْ سَرَاباً |
'Inna Jahannama Kānat Mirşādāan  | 078-021 ገሀነም መጠባበቂያ (ስፍራ) ናት፡፡ | إِنَّ جَهَنَّمَ كَانَتْ مِرْصَاداً |
Lilţţāghīna Ma'ābāan  | 078-022 ለሕግ ተላላፊዎች መመለሻ ስትኾን፡፡ | لِلْطَّاغِينَ مَآباً |
Lābithīna Fīhā 'Aĥqābāan  | 078-023 በውስጧ ብዙን ዘመናት ነዋሪዎች ሲኾኑ፤ | لاَبِثِينَ فِيهَا أَحْقَاباً |
Lā Yadhūqūna Fīhā Bardāan Wa Lā Sharābāan  | 078-024 በውስጧ ቅዝቃዜንም መጠጥንም አይቀምሱም፡፡ | لاَ يَذُوقُونَ فِيهَا بَرْداً وَلاَ شَرَاباً |
'Illā Ĥamīmāan Wa Ghassāqāan  | 078-025 ግን ሙቅ ውሃንና እዥን (ይቀምሳሉ)፡፡ | إِلاَّ حَمِيماً وَغَسَّاقاً |
Jazā'an Wifāqāan  | 078-026 ተስማሚን ምንዳ ይምመነዳሉ፡፡ | جَزَاءً وِفَاقاً |
'Innahum Kānū Lā Yarjūna Ĥisābāan  | 078-027 እነርሱ ምርመራን የማይፈሩ ነበሩና፡፡ | إِنَّهُمْ كَانُوا لاَ يَرْجُونَ حِسَاباً |
Wa Kadhdhabū Bi'āyātinā Kidhdhābāan  | 078-028 በአንቀጾቻችንም ማስተባበልን አስተባበሉና፡፡ | وَكَذَّبُوا بِآيَاتِنَا كِذَّاباً |
Wa Kulla Shay'in 'Aĥşaynāhu Kitābāan  | 078-029 ነገሩንም ሁሉ የተጻፈ ሲኾን አጠቃለልነው፡፡ | وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ كِتَاباً |
Fadhūqū Falan Nazīdakum 'Illā `Adhābāan  | 078-030 ቅመሱም ቅጣትንም እንጅ (ሌላን) አንጨምራችሁም (ይባላሉ)፡፡ | فَذُوقُوا فَلَنْ نَزِيدَكُمْ إِلاَّ عَذَاباً |
'Inna Lilmuttaqīna Mafāzāan  | 078-031 ለጥንቁቆቹ መዳኛ ስፍራ አልላቸው፡፡ | إِنَّ لِلْمُتَّقِينَ مَفَازاً |
Ĥadā'iqa Wa 'A`nābāan  | 078-032 አትክልቶችና ወይኖችም፡፡ | حَدَائِقَ وَأَعْنَاباً |
Wa Kawā`iba 'Atrābāan  | 078-033 እኩያዎች የኾኑ ጡተ ጉቻማዎችም፡፡ | وَكَوَاعِبَ أَتْرَاباً |
Wa Ka'sāan Dihāqāan  | 078-034 የተሞሉ ብርጭቆዎችም፡፡ | وَكَأْساً دِهَاقاً |
Lā Yasma`ūna Fīhā Laghwan Wa Lā Kidhdhābāan  | 078-035 በውስጧ ትርፍ ቃልንም ማስዋሸትንም አይሰሙም፡፡ | لاَ يَسْمَعُونَ فِيهَا لَغْواً وَلاَ كِذَّاباً |
Jazā'an Min Rabbika `Aţā'an Ĥisābāan  | 078-036 ከጌታህ የኾነን ምንዳ በቂ ስጦታን (ተሰጡ)፡፡ | جَزَاءً مِنْ رَبِّكَ عَطَاءً حِسَاباً |
Rabbi As-Samāwāti Wa Al-'Arđi Wa Mā Baynahumā Ar-Raĥmāni Lā Yamlikūna Minhu Khiţābāan  | 078-037 የሰማያትና የምድር በመካከላቸውም ያለው ሁሉ ጌታ በጣም አዛኝ ከኾነው (ተመነዱ)፡፡ ከእርሱ ጋር መነጋገርን አይችሉም፡፡ | رَبِّ السَّمَاوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا الرَّحْمَنِ لاَ يَمْلِكُونَ مِنْهُ خِطَاباً |
Yawma Yaqūmu Ar-Rūĥu Wa Al-Malā'ikatu Şaffāan Lā Yatakallamūna 'Illā Man 'Adhina Lahu Ar-Raĥmānu Wa Qāla Şawābāan  | 078-038 መንፈሱ (ጂብሪል) መላእክቶቹም የተሰለፉ ኾነው በሚቆሙ ቀን አል-ረሕማን ለእርሱ የፈቀደለትና ትክክለኛን ቃል ያለ ሰው ቢኾን እንጅ (መነጋገርን አይችሉም)፡፡ | يَوْمَ يَقُومُ الرُّوحُ وَالْمَلاَئِكَةُ صَفّاً لاَ يَتَكَلَّمُونَ إِلاَّ مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَنُ وَقَالَ صَوَاباً |
Dhālika Al-Yawmu Al-Ĥaqqu Faman Shā'a Attakhadha 'Ilá Rabbihi Ma'ābāan  | 078-039 ይህ የተረጋገጠው ቀን ነው፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መመለስን ይይዛል፡፡ | ذَلِكَ الْيَوْمُ الْحَقُّ فَمَنْ شَاءَ اتَّخَذَ إِلَى رَبِّهِ مَآباً |
'Innā 'Andharnākum `Adhābāan Qarībāan Yawma Yanžuru Al-Mar'u Mā Qaddamat Yadāhu Wa Yaqūlu Al-Kāfiru Yā Laytanī Kuntu Turābāan  | 078-040 እኛ ሰው ሁሉ እጆቹ ያስቀደሙትን በሚያይበትና ከሓዲውም ዋ ምኞቴ! ምንነው ዐፈር በኾንኩ በሚልበት ቀን ቅርብ የኾነን ቅጣት አስጠነቀቅናችሁ፡፡ | إِنَّا أَنذَرْنَاكُمْ عَذَاباً قَرِيباً يَوْمَ يَنظُرُ الْمَرْءُ مَا قَدَّمَتْ يَدَاهُ وَيَقُولُ الْكَافِرُ يَالَيْتَنِي كُنتُ تُرَاباً |