76) Sūrat Al-'Inn

Printed format

76) سُورَة الإنسَان

Hal 'Atá `Alá Al-'Insāni Ĥīnun Mina Ad-Dahri Lam Yakun Shay'āan Madhkūrāan 076-001 በሰው ላይ የሚታወስ ነገር ሳይኾን ከዘመናት የተወሰነ ጊዜ በእርግጥ አልፎበታል፡፡ هَلْ أَتَى عَلَى ا‍لإِن‍س‍‍َ‍ا‍نِ ح‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٌ مِنَ ا‍لدَّهْ‍‍ر‍ِ لَمْ يَكُ‍‍ن‍ْ شَيْئا‍ً مَذْكُورا‍ً
'Innā Khalaq Al-'Insāna Min Nuţfatin 'Amshājin Nabtalīhi Faja`alnāhu Samī`āan Başīrāan 076-002 እኛ ሰውን (በሕግ ግዳጅ) የምንሞከረው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َا خَلَ‍‍ق‍‍ْنَا ا‍لإِن‍س‍‍َ‍ا‍نَ مِ‍‍ن‍ْ نُ‍‍ط‍‍ْفَةٍ أَمْش‍‍َ‍ا‍ج‍‍‍ٍ نَ‍‍ب‍‍ْتَل‍‍ِ‍ي‍هِ فَجَعَلْن‍‍َ‍ا‍هُ سَمِيعا‍ً بَصِيرا‍ً
'Innā Hadaynāhu As-Sabīla 'Immā Shākirāan Wa 'Immā Kafūrāan 076-003 እኛ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሓዲ ሲኾን መንገዱን መራነው፤ (ገለጽንለት)፡፡ إِ‍نّ‍‍َا هَدَيْن‍‍َ‍ا‍هُ ا‍لسَّب‍‍ِ‍ي‍لَ إِ‍مّ‍‍َا شَاكِرا‍ً وَإِ‍مّ‍‍َا كَفُورا‍ً
'Innā 'A`tadnā Lilkāfirīna Salāsilāan Wa 'Aghlālāan Wa Sa`īrāan 076-004 እኛ ለከሓዲዎች ሰንሰሎቶችንና እንዛዝላዎችን፣ እሳትንም አዘጋጅተናል፡፡ إِ‍نّ‍‍َ‍‍ا‍ أَعْتَ‍‍د‍‍ْنَا لِلْكَافِ‍‍ر‍‍ِي‍نَ سَلاَسِلا‍ً وَأَغْلاَلا‍ً وَسَعِيرا‍ً
'Inna Al-'Abrāra Yashrabūna Min Ka'sin Kāna Mizājuhā Kāfūrāan 076-005 በጎ አድራጊዎች መበረዣዋ ካፉር ከኾነች ጠጅ ይጠጣሉ፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لأَ‍ب‍‍ْر‍َا‍رَ يَشْرَب‍‍ُ‍و‍نَ مِ‍‍ن‍ْ كَأْس‍‍‍ٍ ك‍‍َ‍ا‍نَ مِزَاجُهَا كَافُورا‍ً
`Aynāan Yashrabu Bihā `Ibādu Al-Lahi Yufajjirūnahā Tafjīrāan 076-006 ከእርሷ የአላህ ባሮች የሚጠጡላት (ወደፈለጉበት) ማንቧቧትን የሚያንቧቧት ከኾነች ምንጭ (ይጠጣሉ)፡፡ عَيْنا‍ً يَشْرَبُ بِهَا عِب‍‍َ‍ا‍دُ ا‍للَّهِ يُفَجِّرُونَهَا تَفْجِيرا‍ً
Yūfūna Bin-Nadhri Wa Yakhāfūna Yawmāan Kāna Sharruhu Mustaţīrāan 076-007 (ዛሬ) በስለታቸው ይሞላሉ፡፡ መከራው ተሰራጪ የኾነንም ቀን ይፈራሉ፡፡ يُوف‍‍ُ‍و‍نَ بِ‍‍ا‍ل‍‍ن‍ّ‍‍َذْ‍ر‍ِ وَيَخَاف‍‍ُ‍و‍نَ يَوْما‍ً ك‍‍َ‍ا‍نَ شَرُّهُ مُسْتَطِيرا‍ً
Wa Yuţ`imūna Aţ-Ţa`āma `Alá Ĥubbihi Miskīnāan Wa Yatīmāan Wa 'Asīrāan 076-008 ምግብንም ከመውደዳቸው ጋር ለድኻ፣ ለየቲምም፣ ለምርኮኛም ለእስረኛም ያበላሉ፡፡ وَيُ‍‍ط‍‍ْعِم‍‍ُ‍و‍نَ ا‍لطَّع‍‍َ‍ا‍مَ عَلَى حُبِّهِ مِسْكِينا‍ً وَيَتِيما‍ً وَأَسِيرا‍ً
'Innamā Nuţ`imukum Liwajhi Al-Lahi Lā Nurīdu Minkum Jazā'an Wa Lā Shukūrāan 076-009 آ«የምናበላችሁ ለአላህ ውዴታ ብቻ ነው፡፡ ከእናንተ ዋጋንም ማመስገንንም አንፈልግም፡፡ إِ‍نّ‍‍َمَا نُ‍‍ط‍‍ْعِمُكُمْ لِوَج‍‍ْهِ ا‍للَّهِ لاَ نُ‍‍ر‍‍ِي‍دُ مِ‍‍ن‍‍ْكُمْ جَز‍َا‍ء‍ً وَلاَ شُكُورا‍ً
'Innā Nakhāfu Min Rabbinā Yawmāan `Abūsāan Qamţarīrāan 076-010 آ«እኛ (ፊትን) የሚያጨፈግግን ብርቱ ቀን ከጌታችን እንፈራለንና፤آ» (ይላሉ)፡፡ إِ‍نّ‍‍َا نَخ‍‍َ‍ا‍فُ مِ‍‍ن‍ْ رَبِّنَا يَوْماً عَبُوسا‍ً قَمْطَ‍‍ر‍‍ِيرا‍ً
Fawaqāhumu Al-Lahu Sharra Dhālika Al-Yawmi Wa Laqqāhum Nađratan Wa Surūrāan 076-011 አላህም የዚያን ቀን ክፋት ጠበቃቸው፡፡ (ፊታቸው) ማማርንና መደሰትንም ገጠማቸው፡፡ فَوَقَاهُمُ ا‍للَّهُ شَرَّ ذَلِكَ ا‍لْيَوْمِ وَلَقَّاهُمْ نَضْرَة‍‍‍ً وَسُرُورا‍ً
Wa Jazāhum Bimā Şabarū Jannatan Wa Ĥarīrāan 076-012 በመታገሣቸውም ገነትንና የሐር ልብስን መነዳቸው፡፡ وَجَزَاهُ‍‍م‍ْ بِمَا صَبَرُوا‍ جَ‍‍ن‍ّ‍‍َة‍‍‍ً وَحَ‍‍ر‍‍ِيرا‍ً
Muttaki'īna Fīhā `Alá Al-'Arā'iki Lā Yarawna Fīhā Shamsāan Wa Lā Zamharīrāan 076-013 በውስጧ በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ተደጋፊዎች በውስጧ ፀሐይንም ጨረቃንም የማያዩ ሲኾኑ፡፡ مُتَّكِئ‍‍ِ‍ي‍نَ فِيهَا عَلَى ا‍لأَر‍َا‍ئِكِ لاَ يَرَوْنَ فِيهَا شَمْسا‍ً وَلاَ زَمْهَ‍‍ر‍‍ِيرا‍ً
Wa Dāniyatan `Alayhim Žilāluhā Wa Dhullilat Quţūfuhā Tadhlīlāan 076-014 ዛፎችዋም በእነርሱ ላይ የቀረበች፣ ፍሬዎችዋም (ለለቃሚዎች) መግገራትን የተገራች ስትኾን (ገነትን መነዳቸው)፡፡ وَدَانِيَةً عَلَيْهِمْ ظِلاَلُهَا وَذُلِّلَتْ قُطُوفُهَا تَذْلِيلا‍ً
Wa Yuţāfu `Alayhim Bi'āniyatin Min Fiđđatin Wa 'Akwābin Kānat Qawārīra 076-015 በእነርሱም ላይ ከብር በኾኑ ዕቃዎች (ሰሐኖች) የብርጭቆዎች በኾኑ ኩባያዎችም ይዝዞርባቸዋል፡፡ وَيُط‍‍َ‍ا‍فُ عَلَيْهِ‍‍م‍ْ بِآنِيَة‍‍‍ٍ مِ‍‍ن‍ْ فِضَّة‍‍‍ٍ وَأَكْو‍َا‍ب‍‍‍ٍ كَانَتْ قَوَا‍ر‍‍ِي‍‍ر‍َ
Qawārīra Min Fiđđatin Qaddarūhā Taqdīrāan 076-016 መለካትን የለኳቸው በኾኑ የብር ብርጭቆዎች (ይዝዞርባቸዋል)፡፡ قَوَا‍ر‍‍ِي‍‍ر‍َ مِ‍‍ن‍ْ فِضَّة‍‍‍ٍ قَدَّرُوهَا تَ‍‍ق‍‍ْدِيرا‍ً
Wa Yusqawna Fīhā Ka'sāan Kāna Mizājuhā Zanjabīlāan 076-017 በእርሷም መበረዣዋ ዘንጀቢል የኾነችን ጠጅ ይጠጣሉ፡፡ وَيُسْقَوْنَ فِيهَا كَأْسا‍ً ك‍‍َ‍ا‍نَ مِزَاجُهَا زَن‍جَبِيلا‍ً
`Aynāan Fīhā Tusammá Salsabīlāan 076-018 በውስጧ ያለችውን ሰልሰቢል ተብላ የምትጠራውን ምንጭ፡፡ عَيْنا‍ً فِيهَا تُسَ‍‍م‍ّ‍‍َى سَلْسَبِيلا‍ً
Wa Yaţūfu `Alayhim Wildānun Mukhalladūna 'Idhā Ra'aytahum Ĥasibtahum Lu'ulu'uāan Manthūrāan 076-019 በእነርሱም ላይ (ባሉበት ኹነታ) የሚዘወትሩ ወጣት ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡ ባየሃቸው ጊዜ የተበተነ ሉል ናቸው ብለህ ታስባቸዋለህ፡፡ وَيَط‍‍ُ‍و‍فُ عَلَيْهِمْ وِلْد‍َا‍ن‍‍‍ٌ مُخَلَّد‍ُو‍نَ إِذَا رَأَيْتَهُمْ حَسِ‍‍ب‍‍ْتَهُمْ لُؤْلُؤا‍ً مَ‍‍ن‍ثُورا‍ً
Wa 'Idhā Ra'ayta Thamma Ra'ayta Na`īmāan Wa Mulkāan Kabīrāan 076-020 እዚያም በተመለከትክ ጊዜ ጸጋንና ታላቅ ንግሥናን ታያለህ፡፡ وَإِذَا رَأَيْتَ ثَ‍‍م‍ّ‍‍َ رَأَيْتَ نَعِيما‍ً وَمُلْكا‍ً كَبِيرا‍ً
`Āliyahum Thiyābu Sundusin Khuđrun Wa 'Istabraqun Wa Ĥullū 'Asāwira Min Fiđđatin Wa Saqāhum Rabbuhum Sharābāan Ţahūrāan 076-021 አረንጓዴዎች የኾኑ የቀጭን ሐር ልብሶችና ወፍራም ሐርም በላያቸው ላይ አልለ፡፡ ከብር የኾኑ አንባሮችንም ይሸለማሉ፡፡ ጌታቸውም አጥሪ የኾነን መጠጥ ያጠጣቸዋል፡፡ عَالِيَهُمْ ثِي‍‍َ‍ا‍بُ سُ‍‍ن‍دُسٍ خُضْر‍ٌ وَإِسْتَ‍‍ب‍‍ْرَق‍‍‍ٌ وَحُلُّ‍‍و‍‍ا‍ أَسَاوِ‍ر‍َ مِ‍‍ن‍ْ فِضَّة‍‍‍ٍ وَسَقَاهُمْ رَبُّهُمْ شَرَابا‍ً طَهُورا‍ً
'Inna Hādhā Kāna Lakum Jazā'an Wa Kāna Sa`yukum Mashkūrāan 076-022 آ«ይህ በእርግጥ ለእናንተ ዋጋ ኾነ፡፡ ሥራችሁም ምስጉን ኾነ፤آ» (ይባላሉ)፡፡ إِ‍نّ‍‍َ هَذَا ك‍‍َ‍ا‍نَ لَكُمْ جَز‍َا‍ء‍ً وَك‍‍َ‍ا‍نَ سَعْيُكُ‍‍م‍ْ مَشْكُورا‍ً
'Innā Naĥnu Nazzalnā `Alayka Al-Qur'āna Tanzīlāan 076-023 እኛ ቁርኣንን ባንተ ላይ ማውረድን እኛው አወረድነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َا نَحْنُ نَزَّلْنَا عَلَيْكَ ا‍لْقُرْآنَ تَ‍‍ن‍‍ْزِيلا‍ً
Fāşbir Liĥukmi Rabbika Wa Lā Tuţi` Minhum 'Āthimāan 'Aw Kafūrāan 076-024 ለጌታህ ፍርድም ታገሥ፡፡ ከእነርሱም ኀጢአተኛን ወይም ከሓዲን አትታዘዝ፡፡ فَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ وَلاَ تُطِعْ مِنْهُمْ آثِماً أَوْ كَفُورا‍ً
Wa Adhkur Asma Rabbika Bukratan Wa 'Aşīlāan 076-025 የጌታህንም ስም በጧትና ከቀትር በላይ አውሳ፡፡ وَاذْكُرْ ا‍سْمَ رَبِّكَ بُكْرَة‍‍‍ً وَأَصِيلا‍ً
Wa Mina Al-Layli Fāsjud Lahu Wa Sabbiĥhu Laylāan Ţawīlāan 076-026 ከሌሊቱም ለእርሱ ስገድ፡፡ በረዢም ሌሊትም አወድሰው፡፡ وَمِنَ ا‍للَّيْلِ فَاسْجُ‍‍د‍ْ لَهُ وَسَبِّحْهُ لَيْلا‍ً طَوِيلا‍ً
'Inna Hā'uulā' Yuĥibbūna Al-`Ājilata Wa Yadharūna Warā'ahum Yawmāan Thaqīlāan 076-027 እነዚያ ፈጣኒቱን ዓለም ይወዳሉ፡፡ ከባድን ቀንም በስተፊታቸው ኾኖ ይተዋሉ፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ه‍‍َ‍ا‍ؤُلاَء يُحِبّ‍‍ُ‍و‍نَ ا‍لْعَاجِلَةَ وَيَذَر‍ُو‍نَ وَر‍َا‍ءَهُمْ يَوْما‍ً ثَقِيلا‍ً
Naĥnu Khalaqnāhum Wa Shadadnā 'Asrahum Wa 'Idhā Shi'nā Baddalnā 'Amthālahum Tabdīlāan 076-028 እኛ ፈጠርናቸው፡፡ መለያልያቸውንም አጠነከርን፡፡ በሻንም ጊዜ መሰሎቻቸውን መለወጥን እንለውጣለን፡፡ نَحْنُ خَلَ‍‍ق‍‍ْنَاهُمْ وَشَدَ‍د‍‍ْنَ‍‍ا‍ أَسْرَهُمْ وَإِذَا شِئْنَا بَدَّلْنَ‍‍ا‍ أَمْثَالَهُمْ تَ‍‍ب‍‍ْدِيلا‍ً
'Inna Hadhihi Tadhkiratun Faman Shā'a Attakhadha 'Ilá Rabbihi Sabīlāan 076-029 ይህቺ መገሠጫ ናት፡፡ የሻም ሰው ወደ ጌታው መንገድን ይይዛል፡፡ إِ‍نّ‍‍َ هَذِهِ تَذْكِرَة‍‍‍ٌ فَمَ‍‍ن‍ْ ش‍‍َ‍ا‍ءَ ا‍تَّخَذَ إِلَى رَبِّهِ سَبِيلا‍ً
Wa Mā Tashā'ūna 'Illā 'An Yashā'a Al-Lahu 'Inna Al-Laha Kāna `Alīmāan Ĥakīmāan 076-030 አላህም ካልሻ በስተቀር አትሹም፡፡ አላህ ዐዋቂ ጥበበኛ ነውና፡፡ وَمَا تَش‍‍َ‍ا‍ء‍ُو‍نَ إِلاَّ أَ‍ن‍ْ يَش‍‍َ‍ا‍ءَ ا‍للَّهُ إِ‍نّ‍‍َ ا‍للَّهَ ك‍‍َ‍ا‍نَ عَلِيماً حَكِيما‍ً
Yudkhilu Man Yashā'u Fī Raĥmatihi Wa Až-Žālimīna 'A`adda Lahum `Adhābāan 'Alīmāan 076-031 የሚሻውን ሰው በእዝነቱ ውስጥ ያገባዋል፡፡ በዳዮቹንም (ዝቶባቸዋል)፡፡ ለእነርሱ አሳማሚ ቅጣትን አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ يُ‍‍د‍‍ْخِلُ مَ‍‍ن‍ْ يَش‍‍َ‍ا‍ءُ فِي رَحْمَتِهِ وَا‍لظَّالِم‍‍ِ‍ي‍نَ أَعَدَّ لَهُمْ عَذَاباً أَلِيما‍ً
Next Sūrah