15) Sūrat Al-Ĥijr

Printed format

15) سُورَة الحِجر

'Alif-Lām-Rā Tilka 'Āyātu Al-Kitābi Wa Qur'ānin Mubīnin 015-001 አ.ለ.ረ (አሊፍ ላም ራ) ይህች (አናቅጽ) ከመጽሐፉ አንቀጾችና ገላጭ ከኾነው ቁርኣን ናት፡፡ أَلِف-لَام-رَا تِلْكَ آي‍‍َ‍ا‍تُ ا‍لْكِت‍‍َ‍ا‍بِ وَقُرْآن‍‍‍ٍ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Rubamā Yawaddu Al-Ladhīna Kafarū Law Kānū Muslimīna 015-002 እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ ቀን) ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፡፡ رُبَمَا يَوَدُّ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ كَفَرُوا‍ لَوْ كَانُو‍‍ا‍ مُسْلِم‍‍ِ‍ي‍نَ
Dharhum Ya'kulū Wa Yatamatta`ū Wa Yulhihimu Al-'Amalu Fasawfa Ya`lamūna 015-003 ተዋቸው ይብሉ፤ ይጠቀሙም፡፡ ተስፋም ያዘናጋቸው፡፡ በእርግጥም (መጥፎ ፍጻሜያቸውን) ያውቃሉ፡፡ ذَرْهُمْ يَأْكُلُو‍‍ا‍ وَيَتَمَتَّعُو‍‍ا‍ وَيُلْهِهِمُ ا‍لأَمَلُ فَسَوْفَ يَعْلَم‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Mā 'Ahlaknā Min Qaryatin 'Illā Wa Lahā Kitābun Ma`lūmun 015-004 ማንኛይቱንም ከተማ ለእርሷ የተወሰነ መጽሐፍ (ጊዜያት) ያላት ኾና እንጂ አላጠፋንም፡፡ وَمَ‍‍ا‍ أَهْلَكْنَا مِ‍‍ن‍ْ قَرْيَة‍‍‍ٍ إِلاَّ وَلَهَا كِت‍‍َ‍ا‍ب‍‍‍ٌ مَعْل‍‍ُ‍و‍م‍‍‍ٌ
Mā Tasbiqu Min 'Ummatin 'Ajalahā Wa Mā Yasta'khirūna 015-005 ማንኛይቱም ሕዝብ ጊዜዋን ምንም አትቀድምም፡፡ (ከእርሱ) አይቆዩምም፡፡ مَا تَسْبِقُ مِنْ أُ‍مّ‍‍َةٍ أَجَلَهَا وَمَا يَسْتَأْخِر‍ُو‍نَ
Wa Qālū Yā 'Ayyuhā Al-Ladhī Nuzzila `Alayhi Adh-Dhikru 'Innaka Lamajnūnun 015-006 آ«አንተ ያ በእርሱ ላይ ቁርኣን የተወረደለት ሆይ! አንተ በእርግጥ ዕብድ ነህآ» አሉም፡፡ وَقَالُو‍‍ا‍ يَ‍‍ا‍ أَيُّهَا ا‍لَّذِي نُزِّلَ عَلَيْهِ ا‍لذِّكْرُ إِ‍نّ‍‍َكَ لَمَ‍‍ج‍‍ْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٌ
Law Mā Ta'tīnā Bil-Malā'ikati 'In Kunta Mina Aş-Şādiqīna 015-007 آ«ከእውነተኞቹ እንደ ኾንክ በመላእክት (መስካሪ) ለምን አትመጣንምآ» (አሉ)፡፡ لَوْ مَا تَأْتِينَا بِ‍‍ا‍لْمَلاَئِكَةِ إِ‍ن‍ْ كُ‍‍ن‍‍ْتَ مِنَ ا‍لصَّادِق‍‍ِ‍ي‍نَ
Mā Nunazzilu Al-Malā'ikata 'Illā Bil-Ĥaqqi Wa Mā Kānū 'Idhāan Munžarīna 015-008 መላእክትን በእውነት (በቅጣት) እንጂ አናወርድም፡፡ ያን ጊዜም የሚቆዩ አይደሉም፡፡ مَا نُنَزِّلُ ا‍لْمَلاَئِكَةَ إِلاَّ بِ‍‍ا‍لْحَقِّ وَمَا كَانُ‍‍و‍‍ا‍ إِذا‍ً مُ‍‍ن‍‍ْظَ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
'Innā Naĥnu Nazzalnā Adh-Dhikra Wa 'Innā Lahu Laĥāfižūna 015-009 እኛ ቁርኣንን እኛው አወረድነው፡፡ እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን፡፡ إِ‍نّ‍‍َا نَحْنُ نَزَّلْنَا ا‍لذِّكْرَ وَإِ‍نّ‍‍َا لَهُ لَحَافِظ‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Laqad 'Arsalnā Min Qablika Fī Shiya`i Al-'Awwalīna 015-010 ከአንተም በፊት በነበሩት በመጀመሪያዎቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልክተኞችን) በእርግጥ ልከናል፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ أَرْسَلْنَا مِ‍‍ن‍ْ قَ‍‍ب‍‍ْلِكَ فِي شِيَعِ ا‍لأَوَّل‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Mā Ya'tīhim Min Rasūlin 'Illā Kānū Bihi Yastahzi'ūna 015-011 ማንኛውም መልእክተኛ በእርሱ የሚያላግጡበት ኾነው እንጅ አይመጣቸውም ነበር፡፡ وَمَا يَأْتِيهِ‍‍م‍ْ مِ‍‍ن‍ْ رَس‍‍ُ‍و‍ل‍‍‍ٍ إِلاَّ كَانُو‍‍ا‍ بِهِ يَسْتَهْزِئ‍‍ُ‍و‍نَ
Kadhālika Naslukuhu Fī Qulūbi Al-Mujrimīna 015-012 እንደዚሁ (ማስተባበልን) በአመጸኞቹ ልቦች ውስጥ እናገባዋለን፡፡ كَذَلِكَ نَسْلُكُهُ فِي قُل‍‍ُ‍و‍بِ ا‍لْمُ‍‍ج‍‍ْ‍‍ر‍‍ِم‍‍ِ‍ي‍نَ
Lā Yu'uminūna Bihi Wa Qad Khalat Sunnatu Al-'Awwalīna 015-013 በእርሱ አያምኑበትም፡፡ የቀድሞዎቹም ድርጊት በእርግጥ አልፋለች፤ (እንደጠፉ ይጠፋሉ)፡፡ لاَ يُؤْمِن‍‍ُ‍و‍نَ بِهِ وَقَ‍‍د‍ْ خَلَتْ سُ‍‍ن‍ّ‍‍َةُ ا‍لأَوَّل‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Law Fataĥnā `Alayhim Bābāan Mina As-Samā'i Fažallū Fīhi Ya`rujūna 015-014 በእነርሱም ላይ ከሰማይ ደጃፍን በከፈትንላቸውና በእርሱ ሲወጡ በዋሉ ኖሮ፤ وَلَوْ فَتَحْنَا عَلَيْهِ‍‍م‍ْ بَابا‍ً مِنَ ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ فَظَلُّو‍‍ا‍ ف‍‍ِ‍ي‍هِ يَعْرُج‍‍ُ‍و‍نَ
Laqālū 'Innamā Sukkirat 'Abşārunā Bal Naĥnu Qawmun Masĥūrūna 015-015 آ«የተዘጉት ዓይኖቻችን ናቸው፡፡ እንዲያውም እኛ የተደገመብን ሰዎች ነንآ» ባሉ ነበር፡፡ لَقَالُ‍‍و‍‍ا‍ إِ‍نّ‍‍َمَا سُكِّرَتْ أَ‍ب‍‍ْصَارُنَا بَلْ نَحْنُ قَوْم‍‍‍ٌ مَسْحُور‍ُو‍نَ
Wa Laqad Ja`alnā Fī As-Samā'i Burūjāan Wa Zayyannāhā Lilnnāžirīna 015-016 በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፡፡ ለተመልካቾችም (በከዋክብት) አጊጠናታል፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ جَعَلْنَا فِي ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ بُرُوجا‍ً وَزَيَّ‍‍ن‍ّ‍‍َاهَا لِل‍‍ن‍ّ‍‍َاظِ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
Wa Ĥafižnāhā Min Kulli Shayţānin Rajīmin 015-017 ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል፡፡ وَحَفِظْنَاهَا مِ‍‍ن‍ْ كُلِّ شَيْط‍‍َ‍ا‍ن‍‍‍ٍ رَج‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
'Illā Mani Astaraqa As-Sam`a Fa'atba`ahu Shihābun Mubīnun 015-018 ግን (ወሬ) መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል፡፡ (ያቃጥለዋል)፡፡ إِلاَّ مَنِ ا‍سْتَرَقَ ا‍لسَّمْعَ فَأَتْبَعَهُ شِه‍‍َ‍ا‍ب‍‍‍ٌ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٌ
Wa Al-'Arđa Madadnāhā Wa 'Alqaynā Fīhā Rawāsiya Wa 'Anbatnā Fīhā Min Kulli Shay'in Mawzūnin 015-019 ምድርንም ዘረጋናት፡፡ በውስጧም ኮረብታዎችን ጣልናባት፡፡ በውስጧም (የተለካን) በቃይ ሁሉ አበቀልንባት፡፡ وَالأَرْضَ مَدَ‍د‍‍ْنَاهَا وَأَلْقَيْنَا فِيهَا رَوَاسِيَ وَأَ‍ن‍‍ْبَتْنَا فِيهَا مِ‍‍ن‍ْ كُلِّ شَيْء‍ٍ مَوْز‍ُو‍ن‍‍‍ٍ
Wa Ja`alnā Lakum Fīhā Ma`āyisha Wa Man Lastum Lahu Birāziqīna 015-020 በእርሷም ውስጥ ለእናንተ መኖሪያዎችንና ለእርሱ መጋቢዎቹ ያልኾናችሁትንም (እንስሳትን) አደረግንላችሁ፡፡ وَجَعَلْنَا لَكُمْ فِيهَا مَعَايِشَ وَمَ‍‍ن‍ْ لَسْتُمْ لَهُ بِرَازِق‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa 'In Min Shay'in 'Illā `Indanā Khazā'inuhu Wa Mā Nunazziluhu 'Illā Biqadarin Ma`lūmin 015-021 መካዚኖቹም (መክፈቻቸው) እኛ ዘንድ ያልሆነ ምንም ነገር የለም፡፡ በተወሰነም ልክ እንጂ አናወርደውም፡፡ وَإِ‍ن‍ْ مِ‍‍ن‍ْ شَيْء‍ٍ إِلاَّ عِ‍‍ن‍‍ْدَنَا خَز‍َا‍ئِنُهُ وَمَا نُنَزِّلُهُ إِلاَّ بِقَدَر‍ٍ مَعْل‍‍ُ‍و‍م‍‍‍ٍ
Wa 'Arsalnā Ar-Riyāĥa Lawāqiĥa Fa'anzalnā Mina As-Samā'i Mā'an Fa'asqaynākumūhu Wa Mā 'Antum Lahu Bikhāzinīna 015-022 ነፋሶችንም (ደመናን) ተሸካሚዎች አድርገን ላክን፡፡ ከሰማይም (ከደመና) ዝናብን አወረድን፡፡ እርሱንም አጠጣናችሁ፡፡ እናንተም ለእርሱ አድላቢዎች አይደላችሁም፡፡ وَأَرْسَلْنَا ا‍لرِّي‍‍َ‍ا‍حَ لَوَاقِحَ فَأَ‍ن‍‍ْزَلْنَا مِنَ ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ م‍‍َ‍ا‍ء‍ً فَأَسْقَيْنَاكُم‍‍ُ‍و‍هُ وَمَ‍‍ا‍ أَ‍ن‍‍ْتُمْ لَهُ بِخَازِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa 'Innā Lanaĥnu Nuĥyī Wa Numītu Wa Naĥnu Al-Wārithūna 015-023 እኛም ሕያው የምናደርግና የምንገድል እኛው ብቻ ነን፡፡ እኛም (ፍጡርን ሁሉ ) የምንወርስ (ቀሪ) ነን፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُم‍‍ِ‍ي‍تُ وَنَحْنُ ا‍لْوَا‍ر‍‍ِث‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Laqad `Alim Al-Mustaqdimīna Minkum Wa Laqad `Alim Al-Musta'khirīna 015-024 ከእናንተም ተቀዳሚዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ወደ ኋላም ቀሪዎቹን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ عَلِمْنَا ا‍لْمُسْتَ‍‍ق‍‍ْدِم‍‍ِ‍ي‍نَ مِ‍‍ن‍‍ْكُمْ وَلَقَ‍‍د‍ْ عَلِمْنَا ا‍لْمُسْتَأْخِ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
Wa 'Inna Rabbaka Huwa Yaĥshuruhum 'Innahu Ĥakīmun `Alīmun 015-025 ጌታህም እርሱ ይሰበስባችኋል፡፡ እርሱ ጥበበኛ ዐዋቂ ነውና፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َ رَبَّكَ هُوَ يَحْشُرُهُمْ إِ‍نّ‍‍َهُ حَك‍‍ِ‍ي‍مٌ عَل‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٌ
Wa Laqad Khalaq Al-'Insāna Min Şalşālin Min Ĥama'iin Masnūnin 015-026 ሰውንም ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጥቁር ጭቃ በእርግጥ ፈጠርነው፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ خَلَ‍‍ق‍‍ْنَا ا‍لإِن‍س‍‍َ‍ا‍نَ مِ‍‍ن‍ْ صَلْص‍‍َ‍ا‍ل‍‍‍ٍ مِنْ حَمَإ‍ٍ مَسْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
Wa Al-Jānna Khalaqnāhu Min Qablu Min Nāri As-Samūmi 015-027 ጃንንም (ከሰው) በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡ وَالْج‍‍َ‍ا‍نّ‍‍َ خَلَ‍‍ق‍‍ْن‍‍َ‍ا‍هُ مِ‍‍ن‍ْ قَ‍‍ب‍‍ْلُ مِ‍‍ن‍ْ ن‍‍َ‍ا‍ر‍ِ ا‍لسَّم‍‍ُ‍و‍مِ
Wa 'Idh Qāla Rabbuka Lilmalā'ikati 'Innī Khāliqun Basharāan Min Şalşālin Min Ĥama'iin Masnūnin 015-028 ጌታህም ለመላእክት ባለጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ሰውን ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከሚገማ ጭቃ እፈጥራለሁ፡፡ وَإِذْ ق‍‍َ‍ا‍لَ رَبُّكَ لِلْمَلاَئِكَةِ إِ‍نّ‍‍ِي خَالِق‍‍‍ٌ بَشَرا‍ً مِ‍‍ن‍ْ صَلْص‍‍َ‍ا‍ل‍‍‍ٍ مِنْ حَمَإ‍ٍ مَسْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
Fa'idhā Sawwaytuhu Wa Nafakhtu Fīhi Min Rūĥī Faqa`ū Lahu Sājidīna 015-029 (ፍጥረቱን) ባስተካከልኩትና በውስጡ ከመንፈሴ በነፋሁበትም ጊዜ ለእርሱ ሰጋጆች ኾናችሁ ውደቁ፡፡ فَإِذَا سَوَّيْتُهُ وَنَفَخْتُ ف‍‍ِ‍ي‍هِ مِ‍‍ن‍ْ رُوحِي فَقَعُو‍‍ا‍ لَهُ سَاجِد‍ِي‍نَ
Fasajada Al-Malā'ikatu Kulluhum 'Ajma`ūna 015-030 መላእክትም መላውም ተሰብስበው ሰገዱ፡፡ فَسَجَدَ ا‍لْمَلاَئِكَةُ كُلُّهُمْ أَ‍ج‍‍ْمَع‍‍ُ‍و‍نَ
'Illā 'Iblīsa 'Abá 'An Yakūna Ma`a As-Sājidīna 015-031 ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ብቻ ሲቀር፡፡ ከሰጋጆቹ ጋር ከመኾን እንቢ አለ፡፡ إِلاَّ إِ‍ب‍‍ْل‍‍ِ‍ي‍سَ أَبَى أَ‍ن‍ْ يَك‍‍ُ‍و‍نَ مَعَ ا‍لسَّاجِد‍ِي‍نَ
Qāla Yā 'Iblīsu Mā Laka 'Allā Takūna Ma`a As-Sājidīna 015-032 (አላህም) آ«ኢብሊስ ሆይ! ከሰጋጆቹ ጋር የማትኾን ላንተ ምን ምክንያት አለህآ» አለው፡፡ ق‍َا‍لَ يَ‍‍ا إِ‍ب‍‍ْل‍‍ِ‍ي‍سُ مَا لَكَ أَلاَّ تَك‍‍ُ‍و‍نَ مَعَ ا‍لسَّاجِد‍ِي‍نَ
Qāla Lam 'Akun Li'sjuda Libasharin Khalaqtahu Min Şalşālin Min Ĥama'iin Masnūnin 015-033 آ«ከሚቅጨለጨል ሸክላ ከግም ጭቃ ለፈጠርከው ሰው ልሰግድ አይገባኝምآ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ لَمْ أَكُ‍‍ن‍ْ لِأسْجُدَ لِبَشَرٍ خَلَ‍‍ق‍‍ْتَهُ مِ‍‍ن‍ْ صَلْص‍‍َ‍ا‍ل‍‍‍ٍ مِنْ حَمَإ‍ٍ مَسْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
Qāla Fākhruj Minhā Fa'innaka Rajīmun 015-034 (አላህ) አለው آ«ከርሷም ውጣ፡፡ አንተ የተባረርክ እርጉም ነህና፡፡آ» ق‍َا‍لَ فَاخْرُ‍ج‍ْ مِنْهَا فَإِ‍نّ‍‍َكَ رَج‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٌ
Wa 'Inna `Alayka Al-La`nata 'Ilá Yawmi Ad-Dīni 015-035 آ«ባንተ ላይም እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እርግማን አለብህ፡፡آ» وَإِ‍نّ‍‍َ عَلَيْكَ ا‍للَّعْنَةَ إِلَى يَوْمِ ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Qāla Rabbi Fa'anžirnī 'Ilá Yawmi Yub`athūna 015-036 آ«ጌታዬ ሆይ! እንግዲውያስ (ሰዎች) እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ አቆየኝآ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ رَبِّ فَأَ‍ن‍‍ْظِرْنِ‍‍ي إِلَى يَوْمِ يُ‍‍ب‍‍ْعَث‍‍ُ‍و‍نَ
Qāla Fa'innaka Mina Al-Munžarīna 015-037 (አላህም) አለ آ«አንተ ከሚቆዩት ነህ፡፡ ق‍َا‍لَ فَإِ‍نّ‍‍َكَ مِنَ ا‍لْمُ‍‍ن‍‍ْظَ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
'Ilá Yawmi Al-Waqti Al-Ma`lūmi 015-038 آ«እስከታወቀው ወቅት ቀን ድረስ፡፡آ» إِلَى يَوْمِ ا‍لْوَق‍‍ْتِ ا‍لْمَعْل‍‍ُ‍و‍مِ
Qāla Rabbi Bimā 'Aghwaytanī La'uzayyinanna Lahum Al-'Arđi Wa La'ughwiyannahum 'Ajma`īna 015-039 (ኢብሊስ) አለ آ«ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡آ» ق‍َا‍لَ رَبِّ بِمَ‍‍ا‍ أَغْوَيْتَنِي لَأُزَيِّنَ‍‍ن‍ّ‍‍َ لَهُمْ فِي ا‍لأَرْضِ وَلَأُغْوِيَ‍‍ن‍ّ‍‍َهُمْ أَ‍ج‍‍ْمَع‍‍ِ‍ي‍نَ
'Illā `Ibādaka Minhumu Al-Mukhlaşīna 015-040 آ«ከነርሱ ፍጹሞቹ ባሮችህ ብቻ ሲቀሩ፡፡آ» إِلاَّ عِبَادَكَ مِنْهُمُ ا‍لْمُخْلَص‍‍ِ‍ي‍نَ
Qāla Hādhā Şirāţun `Alayya Mustaqīmun 015-041 (አላህም) አለ آ«ይህ በእኔ ላይ (መጠበቁ የተገባ) ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡آ» ق‍َا‍لَ هَذَا صِر‍َا‍طٌ عَلَيَّ مُسْتَق‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٌ
'Inna `Ibādī Laysa Laka `Alayhim Sulţānun 'Illā Mani Attaba`aka Mina Al-Ghāwīna 015-042 آ«እነሆ ባሮቼ በእነሱ ላይ ላንተ ስልጣን የለህም፡፡ ከጠማሞቹ የተከተለህ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡آ» إِ‍نّ‍‍َ عِبَادِي لَيْسَ لَكَ عَلَيْهِمْ سُلْط‍‍َ‍ا‍ن‍‍‍ٌ إِلاَّ مَنِ ا‍تَّبَعَكَ مِنَ ا‍لْغَاو‍ِي‍نَ
Wa 'Inna Jahannama Lamaw`iduhum 'Ajma`īna 015-043 آ«ገሀነምም (ለርሱና ለተከተሉት) ለመላውም በእርግጥ ቀጠሯቸው ናት፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َ جَهَ‍‍ن‍ّ‍‍َمَ لَمَوْعِدُهُمْ أَ‍ج‍‍ْمَع‍‍ِ‍ي‍نَ
Lahā Sab`atu 'Abwābin Likulli Bābin Minhum Juz'un Maqsūmun 015-044 آ«ለእርሷ ሰባት ደጃፎች አሏት፡፡ ለየደጀፉም ሁሉ ከእነሱ የተከፈለ ፋንታ አለ፡፡ لَهَا سَ‍‍ب‍‍ْعَةُ أَ‍ب‍‍ْو‍َا‍ب‍‍‍ٍ لِكُلِّ ب‍‍َ‍ا‍ب‍‍‍ٍ مِنْهُمْ جُزْء‍ٌ مَ‍‍ق‍‍ْس‍‍ُ‍و‍م‍‍‍ٌ
'Inna Al-Muttaqīna Fī Jannātin Wa `Uyūnin 015-045 آ«እነዚያ (ከኀጢአት) የተጠነቀቁት በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لْمُتَّق‍‍ِ‍ي‍نَ فِي جَ‍‍ن‍ّ‍‍َ‍ا‍ت‍‍‍ٍ وَعُي‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
Adkhulūhā Bisalāmin 'Āminīna 015-046 آ«ጸጥተኞች ኾናችሁ በሰላም ግቧት (ይባላሉ)፡፡ ا‍د‍‍ْخُلُوهَا بِسَلاَم‍‍‍ٍ آمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Naza`nā Mā Fī Şudūrihim Min Ghillin 'Ikhwānāan `Alá Sururin Mutaqābilīna 015-047 آ«ባልጋዎችም ላይ ፊት ለፊት የሚቅጣጩ ወንድማማቾች ኾነው በደረቶቻቸው ውስጥ ከቂም ያለውን ሁሉ እናስወግዳለን፡፡ وَنَزَعْنَا مَا فِي صُدُو‍ر‍‍ِهِ‍‍م‍ْ مِنْ غِلّ‍‍‍ٍ إِخْوَاناً عَلَى سُرُر‍ٍ مُتَقَابِل‍‍ِ‍ي‍نَ
Lā Yamassuhum Fīhā Naşabun Wa Mā Hum Minhā Bimukhrajīna 015-048 آ«በእርሷም ውስጥ ድካም አይነካቸውም፡፡ እነሱም ከእርሷ የሚወጡ አይደሉም፡፡آ» لاَ يَمَسُّهُمْ فِيهَا نَصَب‍‍‍ٌ وَمَا هُ‍‍م‍ْ مِنْهَا بِمُخْرَج‍‍ِ‍ي‍نَ
Nabbi' `Ibādī 'Annī 'Anā Al-Ghafūru Ar-Raĥīmu 015-049 ባሮቼን እኔ መሓሪው አዛኙ እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው፡፡ نَبِّئْ عِبَادِي أَ‍نّ‍‍ِ‍‍ي‍ أَنَا ا‍لْغَف‍‍ُ‍و‍رُ ا‍لرَّح‍‍ِ‍ي‍مُ
Wa 'Anna `Adhābī Huwa Al-`Adhābu Al-'Alīmu 015-050 ቅጣቴም እርሱ አሳማሚ ቅጣት መኾኑን (ንገራቸው)፡፡ وَأَ‍نّ‍‍َ عَذَابِي هُوَ ا‍لْعَذ‍َا‍بُ ا‍لأَل‍‍ِ‍ي‍مُ
Wa Nabbi'hum `An Đayfi 'Ibrāhīma 015-051 ከኢብራሂም እንግዶችም (ወሬ) ንገራቸው፡፡ وَنَبِّئْهُمْ عَ‍‍ن‍ْ ضَيْفِ إِ‍ب‍‍ْرَاه‍‍ِ‍ي‍مَ
'Idh Dakhalū `Alayhi Faqālū Salāmāan Qāla 'Innā Minkum Wajilūna 015-052 በእርሱ ላይ በገቡና ሰላም ባሉት ጊዜ የኾነውን (አስታውስ)፡፡ (እርሱም) آ«እኛ ከእናንተ ፈሪዎች ነንآ» አላቸው፡፡ إِذْ دَخَلُو‍‍ا‍ عَلَيْهِ فَقَالُو‍‍ا‍ سَلاَما‍ً ق‍‍َ‍ا‍لَ إِ‍نّ‍‍َا مِ‍‍ن‍‍ْكُمْ وَجِل‍‍ُ‍و‍نَ
Qālū Lā Tawjal 'Innā Nubashshiruka Bighulāmin `Alīmin 015-053 آ«አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ እናበስርሃለንآ» አሉት፡፡ قَالُو‍‍ا‍ لاَ تَوْجَلْ إِ‍نّ‍‍َا نُبَشِّرُكَ بِغُلاَمٍ عَل‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
Qāla 'Abashshartumūnī `Alá 'An Massaniya Al-Kibaru Fabima Tubashshirūna 015-054 آ«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁآ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ أَبَشَّرْتُمُونِي عَلَى أَ‍ن‍ْ مَسَّنِيَ ا‍لْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّر‍ُو‍نَ
Qālū Bashsharnāka Bil-Ĥaqqi Falā Takun Mina Al-Qāniţīna 015-055 آ«በእውነት አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹንآ» አሉ፡፡ قَالُو‍‍ا‍ بَشَّرْن‍‍َ‍ا‍كَ بِ‍‍ا‍لْحَقِّ فَلاَ تَكُ‍‍ن‍ْ مِنَ ا‍لْقَانِط‍‍ِ‍ي‍نَ
Qāla Wa Man Yaqnaţu Min Raĥmati Rabbihi 'Illā Ađ-Đāllūna 015-056 آ«ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነውآ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ وَمَ‍‍ن‍ْ يَ‍‍ق‍‍ْنَطُ مِ‍‍ن‍ْ رَحْمَةِ رَبِّهِ إِلاَّ ا‍لضّ‍‍َ‍ا‍لّ‍‍ُ‍و‍نَ
Qāla Famā Khaţbukum 'Ayyuhā Al-Mursalūna 015-057 آ«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ኧረ ለመኾኑ ነገራችሁ ምንድን ነውآ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ فَمَا خَ‍‍ط‍‍ْبُكُمْ أَيُّهَا ا‍لْمُرْسَل‍‍ُ‍و‍نَ
Qālū 'Innā 'Ursilnā 'Ilá Qawmin Mujrimīna 015-058 آ«እኛ አመጸኞች ወደ ኾኑ ሕዝቦች ተልከናልآ» አሉት፡፡ قَالُ‍‍و‍‍ا‍ إِ‍نّ‍‍َ‍‍ا‍ أُرْسِلْنَ‍‍ا إِلَى قَوْم‍‍‍ٍ مُ‍‍ج‍‍ْ‍‍ر‍‍ِم‍‍ِ‍ي‍نَ
'Illā 'Āla Lūţin 'Innā Lamunajjūhum 'Ajma`īna 015-059 آ«የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ፡፡ (እነርሱን) እኛ ሁላቸውንም በእርግጥ የምናድናቸው ነን፡፡ إِلاَّ آلَ ل‍‍ُ‍و‍ط‍‍‍ٍ إِ‍نّ‍‍َا لَمُنَجُّوهُمْ أَ‍ج‍‍ْمَع‍‍ِ‍ي‍نَ
'Illā Amra'atahu Qaddarnā 'Innahā Lamina Al-Ghābirīna 015-060 آ«ሚስቱ ብቻ ስትቀር፡፡ እርሷን (በቅጣቱ ውስጥ) ከሚቀሩት መኾኗን ወሰነናልآ» (አሉ)፡፡ إِلاَّ ا‍مْرَأَتَهُ قَدَّرْنَ‍‍ا إِ‍نّ‍‍َهَا لَمِنَ ا‍لْغَابِ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
Falammā Jā'a 'Āla Lūţin Al-Mursalūna 015-061 መልክተኞቹም የሉጥን ቤተሰቦች በመጡባቸው ጊዜ፤ فَلَ‍‍م‍ّ‍‍َا ج‍‍َ‍ا‍ءَ آلَ ل‍‍ُ‍و‍ط‍‍‍ٍ ا‍لْمُرْسَل‍‍ُ‍و‍نَ
Qāla 'Innakum Qawmun Munkarūna 015-062 (ሉጥ) آ«እናንተ የተሳታችሁ ሕዝቦች ናችሁآ» አላቸው፡፡ ق‍َا‍لَ إِ‍نّ‍‍َكُمْ قَوْم‍‍‍ٌ مُ‍‍ن‍‍ْكَر‍ُو‍نَ
Qālū Bal Ji'nāka Bimā Kānū Fīhi Yamtarūna 015-063 آ«አይደለም እኛ ሕዝቦችህ በርሱ ይጠራጠሩበት በነበሩት ቅጣት መጣንህآ» አሉት፡፡ قَالُو‍‍ا‍ بَلْ جِئْن‍‍َ‍ا‍كَ بِمَا كَانُو‍‍ا‍ ف‍‍ِ‍ي‍هِ يَمْتَر‍ُو‍نَ
Wa 'Ataynāka Bil-Ĥaqqi Wa 'Innā Laşādiqūna 015-064 آ«እውነትንም ይዘን መጣንህ፡፡ እኛም በእርግጥ እውነተኞች ነን፡፡ وَأَتَيْن‍‍َ‍ا‍كَ بِ‍‍ا‍لْحَقِّ وَإِ‍نّ‍‍َا لَصَادِق‍‍ُ‍و‍نَ
Fa'asri Bi'ahlika Biqiţ`in Mina Al-Layli Wa Attabi` 'Adbārahum Wa Lā Yaltafit Minkum 'Aĥadun Wa Amđū Ĥaythu Tu'umarūna 015-065 ከቤተሰብህም ጋር በሌሊቱ ከፊል ኺድ፡፡ ከኋላቸውም ተከተል፡፡ ከእናንተም አንድም ሰው ወደ ኋላው አይገላመጥ፡፡ ወደ ታዘዛችሁበትም ስፍራ እለፉآ» (አሉት)፡፡ فَأَسْ‍‍ر‍ِ بِأَهْلِكَ بِقِ‍‍ط‍‍ْع‍‍‍ٍ مِنَ ا‍للَّيْلِ وَا‍تَّبِعْ أَ‍د‍‍ْبَارَهُمْ وَلاَ يَلْتَفِتْ مِ‍‍ن‍‍ْكُمْ أَحَد‍ٌ وَا‍مْضُو‍‍ا‍ حَيْثُ تُؤْمَر‍ُو‍نَ
Wa Qađaynā 'Ilayhi Dhālika Al-'Amra 'Anna Dābira Hā'uulā' Maqţū`un Muşbiĥīna 015-066 ወደርሱም ያንን ትእዛዝ አወረድን፡፡ (እርሱም) የእነዚህ (ሕዝቦች) መጨረሻ ያነጉ ሲኾኑ (ሥራቸው) መቆረጥ ነው፡፡ وَقَضَيْنَ‍‍ا إِلَيْهِ ذَلِكَ ا‍لأَمْرَ أَ‍نّ‍‍َ دَابِ‍‍ر‍َ ه‍‍َ‍ا‍ؤُلاَء مَ‍‍ق‍‍ْط‍‍ُ‍و‍ع‍‍‍ٌ مُصْبِح‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Jā'a 'Ahlu Al-Madīnati Yastabshirūna 015-067 የከተማይቱም ሰዎች የሚበሳሰሩ ኾነው መጡ፡፡ وَج‍‍َ‍ا‍ءَ أَهْلُ ا‍لْمَدِينَةِ يَسْتَ‍‍ب‍‍ْشِر‍ُو‍نَ
Qāla 'Inna Hā'uulā' Đayfī Falā Tafđaĥūni 015-068 (ሉጥም) አለ آ«እነዚህ እንግዶቼ ናቸውና አታጋልጡኝ፡፡ ق‍َا‍لَ إِ‍نّ‍‍َ ه‍‍َ‍ا‍ؤُلاَء ضَيْفِي فَلاَ تَفْضَح‍‍ُ‍و‍نِ
Wa Attaqū Al-Laha Wa Lā Tukhzūni 015-069 آ«አላህንም ፍሩ፤ አታሳፍሩኝም፡፡آ» وَاتَّقُو‍‍ا‍ ا‍للَّهَ وَلاَ تُخْز‍ُو‍نِ
Qālū 'Awalam Nanhaka `Ani Al-`Ālamīna 015-070 آ«ከዓለማት (ማንንም እንዳታስተናግድ) አልከለከልንህምንآ» አሉት፡፡ قَالُ‍‍و‍‍ا‍ أَوَلَمْ نَنْهَكَ عَنِ ا‍لْعَالَم‍‍ِ‍ي‍نَ
Qāla Hā'uulā' Banātī 'In Kuntum Fā`ilīna 015-071 (ሉጥም) آ«እነኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው፡፡ ሠሪዎች ብትኾኑ (አግቧቸው)آ» አለ፡፡ ق‍َا‍لَ ه‍‍َ‍ا‍ؤُلاَء بَنَاتِ‍‍ي إِ‍ن‍ْ كُ‍‍ن‍‍ْتُمْ فَاعِل‍‍ِ‍ي‍نَ
La`amruka 'Innahum Lafī Sakratihim Ya`mahūna 015-072 በዕድሜህ እንምላለን እነሱ በእርግጥ በስከራቸው ውስጥ ይዋልላሉ፡፡ لَعَمْرُكَ إِ‍نّ‍‍َهُمْ لَفِي سَكْرَتِهِمْ يَعْمَه‍‍ُ‍و‍نَ
Fa'akhadhat/humu Aş-Şayĥatu Mushriqīna 015-073 ጩኸቲቱም ፀሐይ የወጣችባቸው ሲኾኑ ያዘቻቸው፡፡ فَأَخَذَتْهُمُ ا‍لصَّيْحَةُ مُشْ‍‍ر‍‍ِق‍‍ِ‍ي‍نَ
Faja`alnā `Āliyahā Sāfilahā Wa 'Amţarnā `Alayhim Ĥijāratan Min Sijjīlin 015-074 ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَة‍‍‍ً مِ‍‍ن‍ْ سِجّ‍‍ِ‍ي‍ل‍‍‍ٍ
'Inna Fī Dhālika La'āyātin Lilmutawassimīna 015-075 በዚህ ውስጥ ለተመልካቾች በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡ إِ‍نّ‍‍َ فِي ذَلِكَ لَآي‍‍َ‍ا‍ت‍‍‍ٍ لِلْمُتَوَسِّم‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa 'Innahā Labisabīlin Muqīmin 015-076 እሷም (ከተማይቱ) በቀጥታ መንገድ ላይ ናት፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َهَا لَبِسَب‍‍ِ‍ي‍ل‍‍‍ٍ مُق‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
'Inna Fī Dhālika La'āyatan Lilmu'uminīna 015-077 በዚህ ውስጥ በእርግጥ ለምእምናን መገሰጫ አለ፡፡ إِ‍نّ‍‍َ فِي ذَلِكَ لَآيَة‍‍‍ً لِلْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa 'In Kāna 'Aşĥābu Al-'Aykati Lažālimīna 015-078 እነሆ የአይከት ሰዎችም በእርግጥ በዳዮች ነበሩ፤ وَإِ‍ن‍ْ ك‍‍َ‍ا‍نَ أَصْح‍‍َ‍ا‍بُ ا‍لأَيْكَةِ لَظَالِم‍‍ِ‍ي‍نَ
ntaqamnā Minhum Wa 'Innahumā Labi'imāmin Mubīnin 015-079 ከነሱም ተበቀልን ሁለቱም (የሉጥና የአይከት ሕዝቦች ከተሞች) በእርግጥ በግልጽ መንገድ ላይ ናቸው፡፡ فَا‍ن‍‍ْتَقَمْنَا مِنْهُمْ وَإِ‍نّ‍‍َهُمَا لَبِإِم‍‍َ‍ا‍م‍‍‍ٍ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Wa Laqad Kadhdhaba 'Aşĥābu Al-Ĥijri Al-Mursalīna 015-080 የሒጅርም ሰዎች መልክተኞቹን በእርግጥ አስተባበሉ፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ كَذَّبَ أَصْح‍‍َ‍ا‍بُ ا‍لْحِ‍‍ج‍‍ْ‍‍ر‍ِ ا‍لْمُرْسَل‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa 'Ātaynāhum 'Āyātinā Fakānū `Anhā Mu`rīna 015-081 ተዓምራታችንንም ሰጠናቸው፡፡ ከእርሷም ዘንጊዎች ነበሩ፡፡ وَآتَيْنَاهُمْ آيَاتِنَا فَكَانُو‍‍ا‍ عَنْهَا مُعْ‍‍ر‍‍ِض‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Kānū Yanĥitūna Mina Al-Jibāli Buyūtāan 'Āminīna 015-082 ከኮረብታዎችም ቤቶችን ጸጥተኞች ኾነው ይጠርቡ ነበር፡፡ وَكَانُو‍‍ا‍ يَنْحِت‍‍ُ‍و‍نَ مِنَ ا‍لْجِب‍‍َ‍ا‍لِ بُيُوتا‍ً آمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Fa'akhadhat/humu Aş-Şayĥatu Muşbiĥīna 015-083 ያነጉም ሲኾኑ ጩኸት ያዘቻቸው፤ (ወደሙ)፡፡ فَأَخَذَتْهُمُ ا‍لصَّيْحَةُ مُصْبِح‍‍ِ‍ي‍نَ
Famā 'Aghná `Anhum Mā Kānū Yaksibūna 015-084 ይሠሩትም የነበሩት ሕንጻ ምንም አልጠቀማቸውም፡፡ فَمَ‍‍ا‍ أَغْنَى عَنْهُ‍‍م‍ْ مَا كَانُو‍‍ا‍ يَكْسِب‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Mā Khalaq As-Samāwāti Wa Al-'Arđa Wa Mā Baynahumā 'Illā Bil-Ĥaqqi Wa 'Inna As-Sā`ata La'ātiyatun Fāşfaĥi Aş-Şafĥa Al-Jamīla 015-085 ሰማያትንና ምድርንም በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በእውነት እንጂ (በላግጣ) አልፈጠርንም፡፡ ሰዓቲቱም በእርግጥ መጪ ናት፡፡ መልካምንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡ وَمَا خَلَ‍‍ق‍‍ْنَا ا‍لسَّمَاو‍َا‍تِ وَا‍لأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَ‍‍ا إِلاَّ بِ‍‍ا‍لْحَقِّ وَإِ‍نّ‍‍َ ا‍لسَّاعَةَ لَآتِيَة‍‍‍ٌ فَاصْفَحِ ا‍لصَّفْحَ ا‍لْجَم‍‍ِ‍ي‍لَ
'Inna Rabbaka Huwa Al-Khallāqu Al-`Alīmu 015-086 ጌታህ እርሱ (ያልነበረን) ፈጣሪው ዐዋቂው ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ رَبَّكَ هُوَ ا‍لْخَلاَّقُ ا‍لْعَل‍‍ِ‍ي‍مُ
Wa Laqad 'Ātaynāka Sab`āan Mina Al-Mathānī Wa Al-Qur'āna Al-`Ažīma 015-087 ከሚደጋገሙ የኾኑን ሰባትንና ታላቁንም ቁርኣን (በሙሉ) በእርግጥ ሰጠንህ፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ آتَيْن‍‍َ‍ا‍كَ سَ‍‍ب‍‍ْعا‍ً مِنَ ا‍لْمَثَانِي وَا‍لْقُرْآنَ ا‍لْعَظ‍‍ِ‍ي‍مَ
Lā Tamuddanna `Aynayka 'Ilá Mā Matta`nā Bihi 'Azwājāan Minhum Wa Lā Taĥzan `Alayhim Wa Akhfiđ Janāĥaka Lilmu'uminīna 015-088 ከእነርሱ (ከከሓዲዎች) ብዙዎችን ወገኖች በእርሱ ወደ አጣቀምንበት ጸጋ ዓይኖችህን አትዘርጋ፡፡ በእነሱም ላይ (ባያምኑ) አትዘን፡፡ ክንፍህንም ለምእምናን አለዝብ፡፡ لاَ تَمُدَّ‍‍ن‍ّ‍‍َ عَيْنَيْكَ إِلَى مَا مَتَّعْنَا بِهِ أَزْوَاجا‍ً مِنْهُمْ وَلاَ تَحْزَنْ عَلَيْهِمْ وَا‍خْفِضْ جَنَاحَكَ لِلْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Qul 'Innī 'Anā An-Nadhīru Al-Mubīnu 015-089 በልም آ«እኔ ግልጽ አስፈራሪው እኔ ነኝ፡፡آ» وَقُلْ إِ‍نّ‍‍ِ‍‍ي‍ أَنَا ا‍ل‍‍ن‍ّ‍‍َذ‍ِي‍‍ر‍ُ ا‍لْمُب‍‍ِ‍ي‍نُ
Kamā 'Anzalnā `Alá Al-Muqtasimīna 015-090 (ሰዎችን ለማገድ የመካን በሮች) በተከፋፈሉት ላይ እንደ አወረድነው (በኾነ ቅጣት አሰፈራሪያችሁ ነኝ በል)፡፡ كَمَ‍‍ا‍ أَ‍ن‍‍ْزَلْنَا عَلَى ا‍لْمُ‍‍ق‍‍ْتَسِم‍‍ِ‍ي‍نَ
Al-Ladhīna Ja`alū Al-Qur'āna `Iđīna 015-091 (እነርሱም) እነዚያ ቁርኣንንን ክፍልፍሎች ያደረጉ ናቸው፡፡ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ جَعَلُو‍‍ا‍ ا‍لْقُرْآنَ عِض‍‍ِ‍ي‍نَ
Fawarabbika Lanas'alannahum 'Ajma`īna 015-092 በጌታህም እንምላለን፡፡ ሁላቸውንም እንጠይቃቸዋለን፤ فَوَرَبِّكَ لَنَسْأَلَ‍‍ن‍ّ‍‍َهُمْ أَ‍ج‍‍ْمَع‍‍ِ‍ي‍نَ
`Ammā Kānū Ya`malūna 015-093 ይሠሩት ከነበሩት ነገር ሁሉ፡፡ عَ‍‍م‍ّ‍‍َا كَانُو‍‍ا‍ يَعْمَل‍‍ُ‍و‍نَ
Fāşda` Bimā Tu'umaru Wa 'A`riđ `Ani Al-Mushrikīna 015-094 የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለጽ፡፡ አጋሪዎችንም ተዋቸው፡፡ فَاصْدَعْ بِمَا تُؤْمَرُ وَأَعْ‍‍ر‍‍ِضْ عَنِ ا‍لْمُشْ‍‍ر‍‍ِك‍‍ِ‍ي‍نَ
'Innā Kafaynāka Al-Mustahzi'īna 015-095 ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንሃል፡፡ إِ‍نّ‍‍َا كَفَيْن‍‍َ‍ا‍كَ ا‍لْمُسْتَهْزِئ‍‍ِ‍ي‍نَ
Al-Ladhīna Yaj`alūna Ma`a Al-Lahi 'Ilahāan 'Ākhara Fasawfa Ya`lamūna 015-096 (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፡፡ በእርግጥም (ፍጻሜያቸውን) ወደፊት ያውቃሉ፡፡ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ يَ‍‍ج‍‍ْعَل‍‍ُ‍و‍نَ مَعَ ا‍للَّهِ إِلَها‍ً آخَرَ فَسَوْفَ يَعْلَم‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Laqad Na`lamu 'Annaka Yađīqu Şadruka Bimā Yaqūlūna 015-097 አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መኾኑን በእርግጥ እናውቃለን፡፡ وَلَقَ‍‍د‍ْ نَعْلَمُ أَ‍نّ‍‍َكَ يَض‍‍ِ‍ي‍قُ صَ‍‍د‍‍ْرُكَ بِمَا يَقُول‍‍ُ‍و‍نَ
Fasabbiĥ Biĥamdi Rabbika Wa Kun Mina As-Sājidīna 015-098 ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው ከሰጋጆቹም ኹን፡፡ فَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ وَكُ‍‍ن‍ْ مِنَ ا‍لسَّاجِد‍ِي‍نَ
Wa A`bud Rabbaka Ĥattá Ya'tiyaka Al-Yaqīnu 015-099 እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡ وَاعْبُ‍‍د‍ْ رَبَّكَ حَتَّى يَأْتِيَكَ ا‍لْيَق‍‍ِ‍ي‍نُ
Next Sūrah