51) Sūrat Adh-Dhāriyāt

Printed format

51) سُورَة الذَّارِيَات

Wa Adh-Dhāriyāti Dharwan 051-001 መበተንን በታኞች በኾኑት (ነፋሶች)፡፡ وَالذَّا‍ر‍‍ِي‍‍َ‍ا‍تِ ذَرْوا‍ً
Fālĥāmilāti Wiqan 051-002 ከባድ (ዝናምን) ተሸካሚዎች በኾኑትም (ደመናዎች)፡፡ فَالْحَامِلاَتِ وِ‍ق‍‍ْرا‍ً
Fāljāriyāti Yusrāan 051-003 ገር (መንሻለልን) ተንሻላዮች በኾኑትም (መርከቦች)፡፡ فَالْجَا‍ر‍‍ِي‍‍َ‍ا‍تِ يُسْرا‍ً
Fālmuqassimāti 'Aman 051-004 ነገርን ሁሉ አከፋፋዮች በኾኑትም (መላእክት) እምላለሁ፡፡ فَالْمُقَسِّم‍‍َ‍ا‍تِ أَمْرا‍ً
'Innamā Tū`adūna Laşādiqun 051-005 የምትቀጠሩት (ትንሣኤ) እውነት ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َمَا تُوعَد‍ُو‍نَ لَصَادِ‍ق‍‍ٌ
Wa 'Inna Ad-Dīna Lawāqi`un 051-006 (እንደየሥራው) ዋጋን ማግኘትም፤ ኋኝ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡ وَإِ‍نّ‍‍َ ا‍لدّ‍ِي‍نَ لَوَاقِع‍‍‍ٌ
Wa As-Samā'i Dhāti Al-Ĥubuki 051-007 የ(ከዋክብት) መንገዶች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡ وَالسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ ذ‍َا‍تِ ا‍لْحُبُكِ
'Innakum Lafī Qawlin Mukhtalifin 051-008 እናንተ (የመካ ሰዎች) በተለያየ ቃል ውስጥ ናችሁ፡፡ إِ‍نّ‍‍َكُمْ لَفِي قَوْل‍‍‍ٍ مُخْتَلِف‍‍‍ٍ
Yu'ufaku `Anhu Man 'Ufika 051-009 ከርሱ የሚዝዞር ሰው ይዝዞራል፡፡ يُؤْفَكُ عَنْهُ مَنْ أُفِكَ
Qutila Al-Kharrāşūna 051-010 በግምት የሚናገሩ ውሸታሞች ተረገሙ፡፡ قُتِلَ ا‍لْخَرَّاص‍‍ُ‍و‍نَ
Al-Ladhīna HumGhamratin Sāhūna 051-011 እነዚያ እነርሱ በሚሸፍን ስሕተተ ውስጥ ዘንጊዎች የኾኑት፡፡ ا‍لَّذ‍ِي‍نَ هُمْ فِي غَمْرَة‍‍‍ٍ سَاه‍‍ُ‍و‍نَ
Yas'alūna 'Ayyāna Yawmu Ad-Dīni 051-012 የዋጋ መስጫው ቀን መቼ እንደ ኾነ ይጠይቃሉ፡፡ يَسْأَل‍‍ُ‍و‍نَ أَيّ‍‍َ‍ا‍نَ يَوْمُ ا‍لدّ‍ِي‍نِ
Yawma Hum `Alá An-Nāri Yuftanūna 051-013 (እነርሱ) በእሳት ላይ በሚፈተኑበት ቀን ነው፡፡ يَوْمَ هُمْ عَلَى ا‍ل‍‍ن‍ّ‍‍َ‍ا‍ر‍ِ يُفْتَن‍‍ُ‍و‍نَ
Dhūqū Fitnatakumdhā Al-Ladhī Kuntum Bihi Tasta`jilūna 051-014 آ«መከራችሁን ቅመሱ፤ ይህ ያ በእርሱ ትቻኮሉበት የነበራችሁት ነውآ» (ይባላሉ)፡፡ ذُوقُو‍‍ا‍ فِتْنَتَكُمْ هَذَا ا‍لَّذِي كُ‍‍ن‍تُ‍‍م‍ْ بِهِ تَسْتَعْجِل‍‍ُ‍و‍نَ
'Inna Al-Muttaqīna Fī Jannātin Wa `Uyūnin 051-015 አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍لْمُتَّق‍‍ِ‍ي‍نَ فِي جَ‍‍ن‍ّ‍‍َ‍ا‍ت‍‍‍ٍ وَعُي‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٍ
'Ākhidhīna Mā 'Ātāhum Rabbuhum 'Innahum Kānū Qabla Dhālika Muĥsinīna 051-016 ያንን ጌታቸው የሰጣቸውን ተቀባዮች ኾነው፤ (በገነት ውስጥ ይኾናሉ)፡፡ እነርሱ ከዚህ በፊት መልካም ሰሪዎች ነበሩና፡፡ آخِذ‍ِي‍نَ مَ‍‍ا آتَاهُمْ رَبُّهُمْ إِ‍نّ‍‍َهُمْ كَانُو‍‍ا‍ قَ‍‍ب‍‍ْلَ ذَلِكَ مُحْسِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Kānū Qalīlāan Mina Al-Layli Mā Yahja`ūna 051-017 ከሌሊቱ ጥቂትን ብቻ ይተኙ ነበሩ፡፡ كَانُو‍‍ا‍ قَلِيلا‍ً مِنَ ا‍للَّيْلِ مَا يَهْجَع‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Bil-'Asĥāri Hum Yastaghfirūna 051-018 በሌሊቱ መጨረሻዎችም እነርሱ ምሕረትን ይለምናሉ፡፡ وَبِالأَسْح‍‍َ‍ا‍ر‍ِ هُمْ يَسْتَغْفِر‍ُو‍نَ
Wa Fī 'Amwālihim Ĥaqqun Lilssā'ili Wa Al-Maĥrūmi 051-019 በገንዘቦቻቸውም ውስጥ ለለማኝና (ከልመና) ለተከለከለም (በችሮታቸው) መብት አልለ፡፡ وَفِ‍‍ي‍ أَمْوَالِهِمْ حَقّ‍‍‍ٌ لِلسّ‍‍َ‍ا‍ئِلِ وَا‍لْمَحْر‍ُو‍مِ
Wa Fī Al-'Arđi 'Āyātun Lilmūqinīna 051-020 በምድርም ውስጥ ለሚያረጋግጡ ሰዎች ምልክቶች አልሉ፡፡ وَفِي ا‍لأَرْضِ آي‍‍َ‍ا‍ت‍‍‍ٌ لِلْمُوقِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Fī 'Anfusikum 'Afalā Tubşirūna 051-021 በነፍሶቻችሁም ውስጥ (ምልክቶች አልሉ)፤ ታዲያ አትመለከቱምን?â€؛ وَفِ‍‍ي‍ أَن‍فُسِكُمْ أَفَلاَ تُ‍‍ب‍‍ْصِر‍ُو‍نَ
Wa Fī As-Samā'i Rizqukum Wa Mā Tū`adūna 051-022 ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡ وَفِي ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ ‍ر‍‍ِزْقُكُمْ وَمَا تُوعَد‍ُو‍نَ
Fawarabbi As-Samā'i Wa Al-'Arđi 'Innahu Laĥaqqun Mithla Mā 'Annakum Tanţiqūna 051-023 በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡ فَوَرَبِّ ا‍لسَّم‍‍َ‍ا‍ءِ وَا‍لأَرْضِ إِ‍نّ‍‍َهُ لَحَقّ‍‍‍ٌ مِثْلَ مَ‍‍ا‍ أَ‍نّ‍‍َكُمْ تَ‍‍ن‍طِق‍‍ُ‍و‍نَ
Hal 'Atāka Ĥadīthu Đayfi 'Ibrāhīma Al-Mukramīna 051-024 የተከበሩት የኢብራሂም እንግዶች ወሬ መጥቶሃልን? هَلْ أَت‍‍َ‍ا‍كَ حَد‍ِي‍ثُ ضَيْفِ إِ‍ب‍‍ْرَاه‍‍ِ‍ي‍مَ ا‍لْمُكْرَم‍‍ِ‍ي‍نَ
'Idh Dakhalū `Alayhi Faqālū Salāmāan Qāla Salāmun Qawmun Munkarūna 051-025 በእርሱ ላይ በገቡና آ«ሰለምآ» ባሉ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ آ«ሰላም ያልታወቃችሁ ሕዝቦች ናችሁ፤آ» አላቸው፡፡ إِذْ دَخَلُو‍‍ا‍ عَلَيْهِ فَقَالُو‍‍ا‍ سَلاَما‍ً ق‍‍َ‍ا‍لَ سَلاَم‍‍‍ٌ قَوْم‍‍‍ٌ مُ‍‍ن‍كَر‍ُو‍نَ
Farāgha 'Ilá 'Ahlihi Fajā'a Bi`ijlin Samīnin 051-026 ወደ ቤተሰቡም ተዘነበለ፤آ» ወዲያውም የሰባ ወይፈንን አመጣ፡፡ فَر‍َا‍غَ إِلَى أَهْلِهِ فَج‍‍َ‍ا‍ءَ بِعِ‍‍ج‍‍ْل‍‍‍ٍ سَم‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Faqarrabahu 'Ilayhim Qāla 'Alā Ta'kulūna 051-027 ወደእነርሱም (አርዶና ጠብሶ) አቀረበው፡፡ آ«አትበሉም ወይ?آ» አላቸው፡፡ فَقَرَّبَهُ إِلَيْهِمْ ق‍‍َ‍ا‍لَ أَلاَ تَأْكُل‍‍ُ‍و‍نَ
Fa'awjasa Minhum Khīfatan Qālū Lā Takhaf Wa Bashsharūhu Bighulāmin `Alīmin 051-028 ከእነርሱ መፍራትንም በልቡ አሳደረ፡፡ آ«አትፍራآ» አሉት፡፡ በዐዋቂ ወጣት ልጅም አበሰሩት፡፡ فَأَوْجَسَ مِنْهُمْ خِيفَة‍‍‍ً قَالُو‍‍ا‍ لاَ تَخَفْ وَبَشَّر‍ُو‍هُ بِغُلاَمٍ عَل‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٍ
Fa'aqbalati Amra'atuhu Fī Şarratin Faşakkat Wajhahā Wa Qālat `Ajūzun `Aqīmun 051-029 ሚስቱም እየጮኸች መጣች፡፡ ፊቷንም መታች፡፡ آ«መካን አሮጊት ነኝآ» አለችም፡፡ فَأَ‍ق‍‍ْبَلَتِ ا‍مْرَأَتُهُ فِي صَرَّة‍‍‍ٍ فَصَكَّتْ وَج‍‍ْهَهَا وَقَالَتْ عَج‍‍ُ‍و‍زٌ عَق‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٌ
Qālū Kadhāliki Qāla Rabbuki 'Innahu Huwa Al-Ĥakīmu Al-`Alīmu 051-030 እንደዚህ ጌታሽ ብሏል፡፡ آ«እነሆ እርሱ ጥበባ ዐዋቂ ነውናآ» አሏት፡፡ قَالُو‍‍ا‍ كَذَلِكِ ق‍‍َ‍ا‍لَ رَبُّكِ إِ‍نّ‍‍َهُ هُوَ ا‍لْحَك‍‍ِ‍ي‍مُ ا‍لْعَل‍‍ِ‍ي‍مُ
Qāla Famā Khaţbukum 'Ayyuhā Al-Mursalūna 051-031 آ«እናንተ መልክተኞች ሆይ! ታዲያ ነገራችሁ ምንድን ነው?آ» አላቸው፡፡ ق‍َا‍لَ فَمَا خَ‍‍ط‍‍ْبُكُمْ أَيُّهَا ا‍لْمُرْسَل‍‍ُ‍و‍نَ
Qālū 'Innā 'Ursilnā 'Ilá Qawmin Mujrimīna 051-032 (እነርሱም) አሉ፡- آ«እኛ ወደ አመጸኞች ሕዝቦች ተልከናል፡፡آ» قَالُ‍‍و‍‍ا‍ إِ‍نّ‍‍َ‍‍ا‍ أُرْسِلْنَ‍‍ا إِلَى قَوْم‍‍‍ٍ مُ‍‍ج‍‍ْ‍‍ر‍‍ِم‍‍ِ‍ي‍نَ
Linursila `Alayhim Ĥijāratan Min Ţīnin 051-033 በእነርሱ ላይ ከጭቃ የኾኑን ድንጋዮች ልንለቅባቸው (ተላክን)፡፡ لِنُرْسِلَ عَلَيْهِمْ حِجَارَة‍‍‍ً مِ‍‍ن‍ْ ط‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Musawwamatan `Inda Rabbika Lilmusrifīna 051-034 በጌታህ ዘንድ ለድንበር አላፊዎቹ (በየስማቸው) ምልክት የተደረገባት ስትኾን፡፡ مُسَوَّمَةً عِ‍‍ن‍‍ْدَ رَبِّكَ لِلْمُسْ‍‍ر‍‍ِف‍‍ِ‍ي‍نَ
Fa'akhrajnā Man Kāna Fīhā Mina Al-Mu'uminīna 051-035 ከምእምናንም፤ በእርሷ (በከተማቸው) ውስጥ የነበሩትን አወጣን፡፡ فَأَخْرَ‍ج‍‍ْنَا مَ‍‍ن‍ْ ك‍‍َ‍ا‍نَ فِيهَا مِنَ ا‍لْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Famā Wajadnā Fīhā Ghayra Baytin Mina Al-Muslimīna 051-036 በውስጧም ከሙስሊሞች ከአንድ ቤት (ቤተሰቦች) በስተቀር አላገኘንም፡፡ فَمَا وَجَ‍‍د‍‍ْنَا فِيهَا غَيْرَ بَيْت‍‍‍ٍ مِنَ ا‍لْمُسْلِم‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Taraknā Fīhā 'Āyatan Lilladhīna Yakhāfūna Al-`Adhāba Al-'Alīma 051-037 በውስጧም ለእነዚያ አሳማሚውን ቅጣት ለሚፈሩት ምልክትን አስቀረን፡፡ وَتَرَكْنَا فِيهَ‍‍ا آيَة‍‍‍ً لِلَّذ‍ِي‍نَ يَخَاف‍‍ُ‍و‍نَ ا‍لْعَذ‍َا‍بَ ا‍لأَل‍‍ِ‍ي‍مَ
Wa Fī Mūsá 'Idh 'Arsalnāhu 'Ilá Fir`awna Bisulţānin Mubīnin 051-038 በሙሳም (ወሬ) ውስጥ ወደ ፈርዖን በግልጽ ማስረጃ በላክነው ጊዜ (ምልክትን አደረግን)፡፡ وَفِي مُوسَى إِذْ أَرْسَلْن‍‍َ‍ا‍هُ إِلَى فِرْعَوْنَ بِسُلْط‍‍َ‍ا‍ن‍‍‍ٍ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Fatawallá Biruknihi Wa Qāla Sāĥirun 'Aw Majnūnun 051-039 ከድጋፉ (ከሰራዊቱ) ጋርም (ከእምነት) ዞረ፡፡ (እርሱ) آ«ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነውآ» አለም፡፡ فَتَوَلَّى بِرُكْنِهِ وَق‍‍َ‍ا‍لَ سَاحِرٌ أَوْ مَ‍‍ج‍‍ْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٌ
Fa'akhadhnāhu Wa Junūdahu Fanabadhnāhum Al-Yammi Wa Huwa Mulīmun 051-040 እርሱንም ሰራዊቱንም ያዝናቸው፡፡ እርሱ ተወቃሽ ሲኾን በባሕር ውስጥም ጣልናቸው፡፡ فَأَخَذْن‍‍َ‍ا‍هُ وَجُنُودَهُ فَنَبَذْنَاهُمْ فِي ا‍لْيَ‍‍م‍ّ‍‍ِ وَهُوَ مُل‍‍ِ‍ي‍م‍‍‍ٌ
Wa Fī `Ādin 'Idh 'Arsalnā `Alayhimu Ar-Rīĥa Al-`Aqīma 051-041 በዓድም በእነርሱ ላይ መካንን ነፋስ በላክን ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡ وَفِي ع‍‍َ‍ا‍د‍ٍ إِذْ أَرْسَلْنَا عَلَيْهِمُ ا‍لرّ‍ِي‍حَ ا‍لْعَق‍‍ِ‍ي‍مَ
Mā Tadharu Min Shay'in 'Atat `Alayhi 'Illā Ja`alat/hu Kālrramīmi 051-042 በላዩ ላይ የመጣችበትን ማንኛውንም ነገር እንደ በሰበሰ አጥንት ያደረገችው ብትኾን እንጂ አትተወውም፡፡ مَا تَذَرُ مِ‍‍ن‍ْ شَيْءٍ أَتَتْ عَلَيْهِ إِلاَّ جَعَلَتْهُ كَال‍رَّم‍‍ِ‍ي‍مِ
Wa Fī Thamūda 'Idh Qīla Lahum Tamatta`ū Ĥattá Ĥīnin 051-043 በሰሙድም ለእነርሱ آ«እስከ ጊዜ (ሞታችሁ) ድረስ ተጣቀሙآ» በተባሉ ጊዜ (ምልክት አልለ)፡፡ وَفِي ثَم‍‍ُ‍و‍دَ إِذْ ق‍‍ِ‍ي‍لَ لَهُمْ تَمَتَّعُو‍‍ا‍ حَتَّى ح‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٍ
Fa`ataw `An 'Amri Rabbihim Fa'akhadhat/humu Aş-Şā`iqatu Wa Hum Yanžurūna 051-044 ከጌታቸው ትዕዛዝም ኮሩ፡፡ እነርሱም እያዩ ጩኸት ያዘቻቸው፡፡ فَعَتَوْا عَنْ أَمْ‍‍ر‍ِ رَبِّهِمْ فَأَخَذَتْهُمُ ا‍لصَّاعِقَةُ وَهُمْ يَ‍‍ن‍ظُر‍ُو‍نَ
Famā Astaţā`ū Min Qiyāmin Wa Mā Kānū Muntaşirīna 051-045 መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡ فَمَا ا‍سْتَطَاعُو‍‍ا‍ مِ‍‍ن‍ْ قِي‍‍َ‍ا‍م‍‍‍ٍ وَمَا كَانُو‍‍ا‍ مُ‍‍ن‍تَصِ‍‍ر‍‍ِي‍نَ
Wa Qawma Nūĥin Min Qablu 'Innahum Kānū Qawmāan Fāsiqīna 051-046 የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡ وَقَوْمَ ن‍‍ُ‍و‍ح‍‍‍ٍ مِ‍‍ن‍ْ قَ‍‍ب‍‍ْلُ إِ‍نّ‍‍َهُمْ كَانُو‍‍ا‍ قَوْما‍ً فَاسِق‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa As-Samā'a Banaynāhā Bi'ayydin Wa 'Innā Lamūsi`ūna 051-047 ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡ وَالسَّم‍‍َ‍ا‍ءَ بَنَيْنَاهَا بِأَيْيد‍ٍ وَإِ‍نّ‍‍َا لَمُوسِع‍‍ُ‍و‍نَ
Wa Al-'Arđa Farashnāhā Fani`ma Al-Māhidūna 051-048 ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!) وَالأَرْضَ فَرَشْنَاهَا فَنِعْمَ ا‍لْمَاهِد‍ُو‍نَ
Wa Min Kulli Shay'in Khalaqnā Zawjayni La`allakum Tadhakkarūna 051-049 ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡ وَمِ‍‍ن‍ْ كُلِّ شَيْءٍ خَلَ‍‍ق‍‍ْنَا زَوْجَيْنِ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّر‍ُو‍نَ
Fafirrū 'Ilá Al-Lahi 'Innī Lakum Minhu Nadhīrun Mubīnun 051-050 آ«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝናآ» (በላቸው)፡፡ فَفِرُّو‍ا‍ إِلَى ا‍للَّهِ إِ‍نّ‍‍ِي لَكُ‍‍م‍ْ مِنْهُ نَذ‍ِي‍ر‍ٌ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٌ
Wa Lā Taj`alū Ma`a Al-Lahi 'Ilahāan 'Ākhara 'Innī Lakum Minhu Nadhīrun Mubīnun 051-051 ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ አስፈራሪ ነኝና፡፡ وَلاَ تَ‍‍ج‍‍ْعَلُو‍‍ا‍ مَعَ ا‍للَّهِ إِلَها‍ً آخَرَ إِ‍نّ‍‍ِي لَكُ‍‍م‍ْ مِنْهُ نَذ‍ِي‍ر‍ٌ مُب‍‍ِ‍ي‍ن‍‍‍ٌ
Kadhālika Mā 'Atá Al-Ladhīna Min Qablihim Min Rasūlin 'Illā Qālū Sāĥirun 'Aw Majnūnun 051-052 (ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) آ«ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነውآ» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡ كَذَلِكَ مَ‍‍ا‍ أَتَى ا‍لَّذ‍ِي‍نَ مِ‍‍ن‍ْ قَ‍‍ب‍‍ْلِهِ‍‍م‍ْ مِ‍‍ن‍ْ رَس‍‍ُ‍و‍ل‍‍‍ٍ إِلاَّ قَالُو‍‍ا‍ سَاحِرٌ أَوْ مَ‍‍ج‍‍ْن‍‍ُ‍و‍ن‍‍‍ٌ
'Atawāşaw Bihi Bal Hum Qawmun Ţāghūna 051-053 በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች ናቸው፡፡ أَتَوَاصَوْا بِهِ بَلْ هُمْ قَوْم‍‍‍ٌ طَاغ‍‍ُ‍و‍نَ
Fatawalla `Anhum Famā 'Anta Bimalūmin 051-054 ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡ فَتَوَلَّ عَنْهُمْ فَمَ‍‍ا‍ أَ‍ن‍‍ْتَ بِمَل‍‍ُ‍و‍م‍‍‍ٍ
Wa Dhakkir Fa'inna Adh-Dhikrá Tanfa`u Al-Mu'uminīna 051-055 ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡ وَذَكِّرْ فَإِ‍نّ‍‍َ ا‍لذِّكْرَى تَ‍‍ن‍فَعُ ا‍لْمُؤْمِن‍‍ِ‍ي‍نَ
Wa Mā Khalaqtu Al-Jinna Wa Al-'Insa 'Illā Liya`budūni 051-056 ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ وَمَا خَلَ‍‍ق‍‍ْتُ ا‍لْجِ‍‍ن‍ّ‍‍َ وَا‍لإِن‍سَ إِلاَّ لِيَعْبُد‍ُو‍نِ
Mā 'Urīdu Minhum Min Rizqin Wa Mā 'Urīdu 'An Yuţ`imūni 051-057 ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡ مَ‍‍ا‍ أُ‍ر‍‍ِي‍دُ مِنْهُ‍‍م‍ْ مِ‍‍ن‍ْ ‍ر‍‍ِزْق‍‍‍ٍ وَمَ‍‍ا‍ أُ‍ر‍‍ِي‍دُ أَ‍ن‍ْ يُ‍‍ط‍‍ْعِم‍‍ُ‍و‍نِ
'Inna Al-Laha Huwa Ar-Razzāqu Dhū Al-Qūwati Al-Matīnu 051-058 አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡ إِ‍نّ‍‍َ ا‍للَّهَ هُوَ ا‍لرَّزّ‍َا‍قُ ذُو ا‍لْقُوَّةِ ا‍لْمَت‍‍ِ‍ي‍نُ
Fa'inna Lilladhīna Žalamū Dhanūbāan Mithla Dhanūbi 'Aşĥābihim Falā Yasta`jilūni 051-059 ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡ ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡ فَإِ‍نّ‍‍َ لِلَّذ‍ِي‍نَ ظَلَمُو‍‍ا‍ ذَنُوبا‍ً مِثْلَ ذَن‍‍ُ‍و‍بِ أَصْحَابِهِمْ فَلاَ يَسْتَعْجِل‍‍ُ‍و‍نِ
Fawaylun Lilladhīna Kafarū Min Yawmihimu Al-Ladhī Yū`adūna 051-060 ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡ فَوَيْل‍‍‍ٌ لِلَّذ‍ِي‍نَ كَفَرُوا‍ مِ‍‍ن‍ْ يَوْمِهِمُ ا‍لَّذِي يُوعَد‍ُو‍نَ
Next Sūrah